19/08/2022
የኢትዮጵ ባንኮች በ2014 የሒሳብ ዓመት
- ከ18ቱ ባንኮች ሁለቱ የመንግስት ሲሆኑ(የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ) 16ቱ ደግሞ የግል ባንኮች ናቸው
- 18ቱም ባንኮች ከታክስና ከሌሎች ተቀናሾች በፊት ያገኙት ትርፍ ከ70 ቢሊዮን ብር በላይ ነው
- ከዚህ ውስጥ የ16ቱ የግል ባንኮች ያገኙት ትርፍ ከ40 ቢሊዮን ብር በላይ ሲሆን ቀሪውን ከ30 ቢሊዮን በላይ ትርፍ ሁለቱ የመንግስት ባንኮች ያስመዘገቡት ነው
- ከአራት ዓመት በፊት በ2011 የሒሳብ ዓመት የባንኮች ቁጥር 18 ሲሆን በዚህ ዓመት መጨረሻ ላይ በኢትይጵያ ያሉት ባንኮች ቁጥር 30 ደርሷል
- እነዚህ ባንኮች በ2011 የነበራቸው የቅርንጫፎች ብዛት 5,564 የነበረ ሲሆን በ2014 መጨረሻ ላይ 8,944 ደርሷል፡፡ ይህም በአራት ዓመት ውስጥ 61 በመቶ ዕድገት አሳይቷል፡፡
- በ2011 የሒሳብ ዓመት አንድ ቅርንጫፍ ለ16,957 ሰው ሲሆን ይህ ቁጥር በ2014 የሒሳብ ዓመት መጨረሻ ላይ ወደ 11,516 ወርዷል፡፡
- ባለፉት አራት ዓመታት ባንኮቹ ከ73 እስከ 108 በመቶ ዕድገት አሳይተዋል፡፡
- የባንኮች አጠቃላይ የሀብት መጠን ባለፉት አራት ዓመታት በአማካይ 24.5 በመቶ እያደገ በ2014 መጨረሻ ላይ 2.5 ትሪሊዮን ብር ደርሷል፡፡
- ይህ አኃዝ ከ2011 የሒሳብ ዓመት ከነበረው የ1.3 ትሪሊዮን ብር የሀብት መጠን ጋር ሲነፃፀር የ92 በመቶ ዕድገት አሳይተዋል
- በ2011 የሒሳብ ዓመት 952.08 ቢሊዮን ብር የነበረው የባንኮች የብድር ክምችት በ2014 መጨረሻ ላይ 1.64 ትሪሊዮን ብር ደርሷል
- በተቀማጭ ገንዘብ ረገድም ባለፉት አራት ዓመታት በአማካይ 25 በመቶ እያደገ መጥቶ አሁን ላይ 1.73 ትሪሊዮን ብር ደርሷል
- የተቀማጭ ገንዘብ መጠን በ2011 የሒሳብ ዓመት ከነበረበት 899.8 ቢሊዮን ብር አንፃር ሲታይ በአራት ዓመታት ውስጥ 93 በመቶ እድገት አሳይቷል፡፡
- በ2011 የሒሳብ ዓመት የሁሉም ባንኮች ካፒታል መጠን 98.9 ቢሊዮን ብር ነበር፡፡ ይህ የካፒታል መጠን በየዓመቱ በአማካይ 27 በመቶ እያደገ መጥቶ በ2014 መጨረሻ ላይ 199.1 ቢሊዮን ብር ደርሷል፡፡
- ባንኮቹ በ2014 የደረሱበት የካፒታል መጠን ከ2011 የሒሳብ ዓመት ከነበረው ጋር ሲነፃፀርም የ101 በመቶ ዕድገት ታይቶበታል
- በባንኮች የተቀማጭ ሒሳብ የከፈቱ ደንበኞች ቁጥርም በ2011 የሒሳብ ዓመት 40.04 ሚሊዮን የበረ ሲሆን በአራት ዓመት ውስጥ በየዓመቱ በአማካይ በ28 በመቶ ዕድገት እያስመዘገበ 2014 ላይ 83.3 ሚሊዮን ደርሷል፡፡ ይህ የ108 በመቶ ዕድገት ታይቶበታል
- በ2011 የሒሳብ ዓመት ሁሉም ባንኮች ከታክስ በኋላ ያስመዘገቡት የትርፍ መጠን 22.48 ቢሊዮን ብር ነው፡፡ በ2012 ደግሞ 21.86 ቢሊዮን ብር ሲያገኙ በ2013 ከታክስ በኋላ ያገኙትን ትርፍ ወደ 33.54 ቢሊዮን ማድረስ ችለዋል፡፡ በ2014 ደግሞ ከታክስ በፊት 49.9 ቢሊዮን ብር ማድረስ ችለዋል፡፡ ይህ የትርፍ መጠን ዕድገት ከ2011 አንፃር ሲታይ የ122 በመቶ ዕድገት ታይቶበታል
- ባለፉት አራት ዓመታት ኢኮኖሚው ላይ ብዙ ጫና ቢኖርም የባንኮች የተበላሸ የብድር መጠን 3.87 በመቶ ነው፡፡
ምንጭ፡- ሪፖርተር ኦገስት 17 ባንኮችን በተመለከተ ከሰራው ዜና ላይ ተጣርቶ የተወሰደ አሃዝ