25/02/2026
የባሕር በር፡- የማይቀረው የትውልድ ድል!
********
ለኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ በታሪካዊ፣ ሕጋዊ እና ፖለቲካዊ ምክንያቶች የተገነባ ፅኑ ሀገራዊ አቋም ነው።
ኢትዮጵያ ለዘመናት የባሕር በር በማጣቷ ምክንያት በኢኮኖሚ፣ በዲፕሎማሲና በደኅንነት ረገድ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ ስትከፍል ቆይታለች። ይህ የታሪክ ማነቆ ተፈትቶ ሀገራችን የሚገባትን ስፍራ የምትይዝበት ጊዜ አሁን ነው!
ለምን የባሕር በር የሕልውና ጥያቄ ሆነ?
ታሪካዊና ሕጋዊ መሰረት፦ ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር ባለቤትና የቀጣናው የንግድ ማዕከል የነበረች የታሪክ ባለቤት ናት። ጥያቄዋም ከዓለም አቀፍ የሕግ መርሆዎችና ከጂኦ-ፖለቲካዊ እውነታዎች ጋር የተጣጣመ ፍትሐዊ ጥያቄ ነው።
የተከፈለው ከፍተኛ ዋጋ፦ ለዘመናት በወደብ ኪራይና በሎጂስቲክስ መስተጓጎል የፈሰሰው ቢሊዮኖች ዶላር የኢትዮጵያን እድገት የገደበ ትልቅ ሰንሰለት ሆኖ ቆይቷል። ይህ የሀብት ፍሰት ለትውልዱ ብልፅግና መዋል ነበረበት።
ሉዓላዊነትና ራስን መቻል፦ የባሕር በር እጦት ሀገራዊ ደኅንነታችንን ለሌሎች ፍላጎት ተጋላጭ አድርጎታል። ራሳችንን ችለን በሉዓላዊነት ለመቆም የራሳችን የባሕር መውጫ መኖሩ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው።
የማይቀረው ስኬት፦ ኢትዮጵያ ይህንን ታሪካዊ ጥያቄ በእርግጠኝነት ታሳካዋለች! ይህ የዛሬው ትውልድ ትልቁ የቤት ሥራና የድል አክሊል ነው። ማነቆዎቻችንን ሰብረን፣ ከጎረቤቶቻችን ጋር በክብርና በጥቅም ተሳስረን የባሕር በር ባለቤት መሆናችን የማይታጠፍ የታሪክ ጉዞ ነው።
የነገዋ ኢትዮጵያ የባሕር በሯን ከፍታ፣ ልጆቿን መግባ፣ ዳግም ለዓለም የምታበራበት ጊዜ ቅርብ ነው!