08/11/2025
የምርጫ ቦርድ የጌታቸው ረዳን 'ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ' ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ለሕዝብ ይፋ አደረገ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዐዋጅ የተሰጠውን ሥልጣን በመጠቀም፣ በአቶ ጌታቸው ረዳ ካሕሳይ አመራር የቀረበለትን የአዲስ ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ለሕዝብ ይፋ ማድረጉን አስታውቋል
ቦርዱ ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት፣ የምዝገባ ጥያቄው የቀረበለት ፓርቲ "ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት)" በሚል ስያሜ ሲሆን፣ በእንግሊዝኛ ደግሞ "Tigray Democratic Solidarity Party (Solidarity)" በመባል ይታወቃል።
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይህን ያደረገው "በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011" መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመመዝገብ ኃላፊነት ስላለው እንደሆነ የገለፀ ሲሆን በዚኹ መሠረት እነአቶ ጌታቸው ረዳ ካሕሳይ “ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) ወይም Tigray Democratic Solidarity Party (Solidarity)“ በሚል ስያሜ ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ያቀረቡ በመሆኑ፤ በዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 68 ንዑስ አንቀጽ 2 እና 3 መሠረት በፓርቲው ስም፣ ዐርማ ወይም ሌሎች ጉዳዮች ተቃውሞ ያለው ሰው፤ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከዛሬ ከጥቅምት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በ14 ቀናት ውስጥ ተቃውሞውን ለቦርዱ ጽሕፈት ቤት እንዲያቀርብ ቦርዱ አሳውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ