Ante Delala አንቴ ደላላ Debre Markos

Ante Delala አንቴ ደላላ Debre Markos Broker at Debre Markos

11/06/2026
06/06/2026

ጥቅጥቅ ባለው ለሊት ጥቅጥቅ ባለው ውድቅት ለምነው ለምነው ምትመጪ ካንጀቴ ዎጠሽየል እዘው ተቀመጭ

04/06/2026

ኤርትራ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆና ተመረጠች

| የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ በ85ኛው መደበኛ ስብሰባው ላይ በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ዙሪያ ያተኮሩ ቁልፍ አጀንዳዎችን የተወያየ ሲሆን፣ በስብሰባውም ለድርጅቱ 81ኛ ጠቅላላ ጉባኤ መሪ የሚሆኑትን አካላት መርጧል።

በዚህም መሰረት የምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ኤርትራ የከፍተኛ አባል ሀገራትን ድምጽ በማግኘት ከጠቅላላ ጉባኤው ምክትል ፕሬዝዳንቶች አንዷ ሆናለች::

ኤርትራ ከተመረጡ ሌሎች 16 አገራት ጋር በመሆን የጸጥታው ምክር ቤት አምስት ቋሚ አባላትን (ቻይና፣ ፈረንሳይ፣ ሩሲያ፣ ብሪታንያ እና አሜሪካ) በመቀላቀል የጠቅላላ ጉባኤውን ቢሮ በጋራ ትመራለች።

በተጨማሪም ከእሷ ጋር እንደ አፍጋኒስታን፣ ፊንላንድ፣ ግብፅ፣ ሊባኖስ፣ ፓራጓይ እና ዚምባብዌ ያሉ ሀገራትም በምክትል ፕሬዝዳንትነት መመረጣቸውን ለመረዳት ተችሏል።

በተመሳሳይ ዕለት በምስጢር በተካሄደው የድምፅ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት፣ የወቅቱ የባንግላዲሽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካሊሉር ራህማን የ81ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል

ሚስተር ራህማን 99 ድምጽ በማግኘት የተመረጡ ሲሆን፣ ተፎካካሪያቸውን የቆጵሮሱን አንድሪያስ ካኩሪስን በ91 ድምጽ አሸንፈዋል። በነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ ሥራቸውን በይፋ የሚረከቡት ተመራጩ ፕሬዝዳንት ካሊሉር ራህማን ከአሸናፊነታቸው በኋላ ባደረጉት ንግግር፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአሁኑ ወቅት ከባድ የፋይናንስ ቀውስ እና ዓለም አቀፍ የእምነት ማጣት ጉድለት እየገጠመው መሆኑን ጠቅሰው፣ አባል ሀገራቱ ድርጅቱ መለወጥና የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚችል በተግባር ማሳየት እንዳለባቸውና በየብስ የሚደረገውን እያንዳንዱን አስተዋጽኦ ውጤታማ በማድረግ የጠፋውን እምነት መመለስ እንደሚገባ አሳስበዋል

ካፒታል ጋዜጣ

04/06/2026

"ሰኔ እና ሰኞ... አይግጠም"
ሰኔ እና ሰኞ አይግጠም የሚለው የቆየ የአባቶቻችን አባባል ዘንድሮም በ 2018 ዓ.ም. በአይናችን ልናየው በትክክል ገጥሟል። ሰኔ 1 ቀን ሰኞ ይውላሎል።
ከ 1979 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ዛሬ... በከፊል እንይ እስኪ..
1)1979 ዓ.ም. ( ዘመነ ማቲዎስ) በ1979 ዓ.ም. ሰኔ እና ሰኞ ሲገጥም አገሪቱ በከባድ ፈተና ውስጥ ነበረች የ1977ቱ ታላቁ ድርቅ መዘዝ እና በወቅቱ የነበረው የዝናብ እጥረት ተከስቶ ነበረ።
2) 1984 ዓ.ም.( ዘመነ ማርቆስ) በዚህ ወቅት ሰኔ እና ሰኞ በድጋሜ ገጠሙ። ህይ ዓመት የሽግግር ወቅት ቀውስ እንደነበረ የታሪክ መዛግብቶች በጥልቀት ያወሱናል። በዚህም ወቅት በመላው አገሪቱ ከፍተኛ የጸጥታ መደፍረስ ና ግጭት ነገሰ።
3) 1990 ዓ.ም. ( ዘመነ ማርቆስ) በዚህም ወቅት ሰኔ እና ሰኞ ሲገጥም በአገሪቱ ላይ ሊላ የደም ምዕራፍ ተከፈተ።በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል የተነሳው እጅግ አስከፊ የነበረው የባድሜ የድንበር ጦርነት በዚሁ አመት ፈነዳ።
4) 1997 ዓ.ም. ( ዘመነ ዮሐንስ) በ 1997 ላይ ደግሞ ታሪኩ ይበልጥ ልብ ሰባሪ ሆኗል።1997 ሰኔ እና ሰኞ ገጠመ። ያ ታዋቂው እና ውጥረት የበዛበት አገራዊ ምርጫ 97 የተካሄደው በዚህ ወቅት ነበር።
5) በ2007 ዓ.ም. (ዘመነ ዮሐንስ) ከ 10 ዓመታት በኋላ በ 2007 ዓ.ም. በድጋሜ በዘመነ ዮሐንስ ሰኔ እና ሰኞ ገጠሙ።
6) 2013 ዓ.ም. (ዘመነ ማርቆስ) በቅርብ ጊዜ ትውስታችን በሆነው በ 2013 ዓ.ም. ሰኔ እና ሰኞ በድጋሜ ገጠሙ። በዚህም ወቀት የጦርነት የጭንቀት የከበሮ ድምፅ የነበረ መሆኑን ሁላችንም እናስታውሳለን።

የታሪክ ፍሰት አያችሁ? አሁን ደግሞ ወደ ዘንድሮ እንምጣ። ዘንድሮ 2018 ዓ.ም. ነው።አመቱም ድጋሜ ዘመነ ማርቆስ ነው! ሰኔ እና ሰኞ ገጥመዋል። እንደ 1997ቱ, እና 2007ቱ ሁሉ:ዘንድሮም ሰኔ እና ሰኞ በዘመነ ማርቆስ ላይ መውደቃቸው ታዘባቸሁ? ታሪክ እራሱን ይደግማል? ወይንስ እኛ ካለፈው ተምረን ራሳችንን እና አገራችንን እንጠብቃለን? የዘንድሮው የሰኔ እና ሰኞ ገጠመኝ ለኢትዮጵያ ወጣቶች የጥንቃቄ የማስተዋል እና የሰላም ጊዜ ይሁንልን።
አባቶቻችን በምክንያት ነው > ያሉት አስተውሉ !

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይጠብቅ!🇪🇹🇪🇹

04/06/2026

''ዳኛዋ ውሳኔ ሲያነቡ በተቀመጡበት በሽጉጥ ተገደሉ'' በፍትሕ አደባባይ የተፈጸመው አስደንጋጭ ጥቃት በዳኛና በከሳሽ ላይ የተሰነዘረ የግድያ ወንጀል

ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ዛሬ ረፋድ ላይ በሆለታ ወልመራ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የተፈጠረው አሳዛኝ ክስተት ''ለፍትህ በተሰበሰቡበት የፍርድ ቤት አዳራሽ ውስጥ በዕለቱ የቤተሰብ ክርክርን ጉዳይ በመመልከት ላይ የነበረችው ዳኛ ወርቄ ፈካንሳ፣ የፍርድ ውሳኔውን እያነበበች ባለችበት ወሳኝ ወቅት ''ተከሳሹ በድንገት ባወጣው ሽጉጥ ዳኛዋን በጥይት በመምታት ህይወታቸውን ቀጥፏል።

በተጨማሪም በችሎቱ ላይ በባለቤቷ ሲከራከሩ የነበሩት ባለቤታቸውም፣ በተከሳሹ በተተኮሰ ጥይት በተመሳሳይ ሁኔታ ህይወታቸው አልፏል።ይህ ድርጊት በሕግ የበላይነት፣ በፍትሕ ሥርዓቱ እና በማኅበረሰቡ ደኅንነት ላይ የተሰነዘረ እጅግ አስደንጋጭ እና አሳዛኝ ጥቃት ነው።

ዳኛ በሰላማዊ መንገድ ፍርድ በሚያነቡበት፣ ከሳሽም ፍትሕ ፍለጋ በተቀመጡበት የችሎት አዳራሽ ውስጥ እንዲህ ዓይነቱ የኃይል እርምጃ መውሰዱ በፍትሕ አካላት ላይ ሊኖር የሚገባውን ከበሬታና ጥበቃ ጥያቄ ውስጥ የሚጥል ነው።

የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥና የሰዎችን መብት ለማስከበር በደጅ ለሚጠባበቁ ዜጎች ሁሉ የፍርድ ቤት ችሎት የመጨረሻው የሰላምና የፍትሕ መጠለያ ተደርጎ ይወሰዳል። ሆኖም ግን አንድ ተከሳሽ የፍርድ ውሳኔ በሚነበብበት ወቅት በችሎት አዳራሽ ውስጥ በፈጸመው አሰቃቂ ጥቃት የዳኛዋን እና የከሳሽን ሕይወት ቀጥፏል።

ይህ ክስተት የሰዎችን ሕይወት መቅጠፉ ብቻ ሳይሆን፣ በአጠቃላይ በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ የተሰነዘረ ከባድ ጥቃት ነው። ዳኛዋ የተከሳሹን የጥፋተኝነትና የቅጣት ውሳኔ በሰላማዊ መንገድ በማንበብ ላይ ሳሉ፣ ተከሳሹ በድንገት በያዘው ስውር የጦር መሣሪያ (ሽጉጥ) በመተኮስ መጀመሪያ የፍርድ ውሳኔውን እያነበቡ የነበሩትን ዳኛ ሕይወት አጥፍቷል።

ድርጊቱ በዚህ ብቻ አላበቃም፤ ተከሳሹ ወዲያውኑ ፊቱን ወደ ከሳሽ በማዞር በጥይት መቶ ገድሏል፤ በጥቂት ሰከንዶች ውስጥ የነበረው የችሎት ሰላማዊ ድባብ ወደ ድንጋጤ፣ ጩኸትና ደም መፋሰስ ተቀይሯል።

አንድ ተከሳሽ ገዳይ መሣሪያ ይዞ እስከ ችሎት አዳራሽ ድረስ መግባት መቻሉ፣ በፍርድ ቤቶች አካባቢ ያለውን የፍተሻ እና የጥበቃ ሥርዓት ምን ያህል የላላ እንደሆነ የሚያሳይ ማረጋገጫ ነው። ''ይህም ሕግን በገዛ እጅ ለመተርጎም መሞከርና በፍትሕ ውሳኔ ላይ በኃይል ማመፅ የማኅበረሰቡን የሰላም እሴት የሚንድ አደገኛ አካሄድ ነው።

ለዳኛ ወርቄ ፈካንሳ ቤተሰቦችና ለሟች ከሳሽ ወዳጅ ዘመዶች መጽናናትን እንመኛለን!!

02/06/2026

እናንተስ በልጅነታችሁ እንዲህ ዳቦ ሰርቃችሁ ቆርሳችሁ ታውቃላችሁ? ወይስ የተቆረሰችውን አይታ እናታችሁ 'ማነው የቆረሰው?' ስትል አሳልፋችሁ የሰጣችሁት ወንድም ወይም እህት አለ?
ትዝታችሁን በኮመንት አጋሩን! 👇🏾🇪🇹
#የልጅነትትዝታ #ኢትዮጵያ #ባህል #ዳቦ #ትዝታ"

28/05/2026
አይሠው መጨረሻው
22/11/2025

አይሠው መጨረሻው

Address

Debre Markos
Debra Markos

Telephone

+251902024444

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ante Delala አንቴ ደላላ Debre Markos posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category