07/03/2023
27/06/2015ዓ.ም የዩኒዬኑ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ፣የቁጥጥር ኮሚቴ የማኔጅመንት አባላትና ባለሙያወች በተገኙበት የሰባት ወር የእቅድ ክንውን አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዷል።
የፋይናንስ። የቁጠባና ብድር ክፍል ኃላፊወች በበጀት አመቱ በ7ወራት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት አፈጻጸማቸው በአምስቱ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ምን ይመስላል የሚለውን ለታዳሚወች ካቀረቡ በኋላ በዩኒዬኑ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢና በዩኒዬኑ ዋና ስራ አስኪያጅ መሪነት ሰፋ ያለ ውይይት ሲካሄድ ቆይቷል።
በዛሬው ውይይት.....
በዋናነት አባል ማህበራትን በመደገፍ፣በመከታተልና በማጠናከር በየወረዳው ሞዴል የሆኑ ኅብረት ስራ ማህበራትን መፍጠር ዘላቂ አስተማማኝ የፋይናንስ ተቋም ሁነን መገኘት አለብን በሚል ነጥብ የጋራ ውይይት ተደርጓል።
በተጨማሪም.....
ከአባላት በቁጠባ ከሚሰበሰቡ ገንዘቦችና ከተለያዩ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በሚገኝ የተዘዋዋሪ ብድር ለአባል ማህበራት ይሰራጫል ተብሎ በተያዘው እቅድ መሰረት እንዲሁም አባላት በጠየቁት ጥያቄ መሰረት የብድር ጥያቄ ያቀረበው ማህበር እየተገመገመ ብድሩ እየተሰራጨ እንደሚገኝ ተጠቁሟል። ይሁን እንጅ የብድር ስርጭቱ የአባላትን ፍላጎት ማርካት እንዲችል ሁሉም የቁጠባና ብድር ባለሙያወች በየወረዳው ያሉ አባል ማህበራት ቁጠባ እንዳያቆራርጡ፣ ከሰብል ሽያጭ የሚገኘውን ገንዘብ በዩኒዬኑ ላይ በመቆጠብ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚጠበቅባቸው መልዕክት ተላልፏል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ...
ለአባል ማህበራት ብድር በሚሰራጭበት ወቅት ተበዳሪወች አስተማማኝ የብድር ዋስትና በማቅረብና ህጋዊ የሆነ የብድር ውል እንዲይዙ በማድረግ ብድሩ እንዲሰራጭ ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ ከተሰራጨ በኋላም ብድሩ ለታለመለት አላማ እንዲውል እንዲሁም በመመለሻ ጊዜው በአግባቡ እንዲመልሱ ባለሙያው የቅርብ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ውዝፍ ዝድር ከመፈጠሩ በፊት ቅድሚያ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ በውይይቱ ላይ ተነስቷል።
በመጨረሻም.....
ዛሬ የቀረበውን የስራ አፈጻጸም ሪፖርት መነሻ በማድረግ በቀሪ ወራቶች በበጀት አመቱ የተያዘውን እቅድ ሙሉ በሙሉ ፈጽሞ ለመገኘት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን በመወጣት ለዩኒዬኑ ስራ መሳካት በጎ አሻራቸውን እንዲያስቀምጡ የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ስብሰባው ተጠናቋል።
ጣና የህዝብ ባንክ!!!
On 27/06/2015, an evaluation of the performance of the seven-month plan was conducted in the presence of the members of the union's executive board, management members of the control committee and experts.
After the officials of the finance, savings and loan department presented to the audience what the performance of the main activities in the 7 months of the fiscal year was like in the five branch offices, a wide discussion was held under the leadership of the chairman of the management board of the union and the general manager of the union.
In today's conversation.....
There was a joint discussion on the point that we should be a sustainable and reliable financial institution by supporting, monitoring and strengthening member associations and creating model cooperatives in each district.
in addition.....
According to the plan that indirect loans from members' savings and various non-governmental organizations will be distributed to the member associations, and based on the questions asked by the members, it is indicated that the loan is being distributed by the association that submitted the loan request. However, a message has been sent that all the savings and loan experts in each district should create awareness so that the member associations in every district do not cut down on savings, so that the money from the sale of crops can be saved and benefited by the union.
Meanwhile...
During the distribution of loans to member associations, the borrowers should be provided with a reliable loan guarantee and have a legal loan contract.
Finally.....
Based on the work performance report presented today, the meeting was concluded by setting a direction for all the stakeholders to do their part and leave a good mark for the success of the work of the Union in the remaining months of the budget year.
Tana Public Bank!!!
www.facebook.com/tanacooprativeunion
www.facebook.com/tana.4361
ጣና ዩኒየን
Tana cosacou