04/01/2026
ጎል ኃ/የተወሰነ የህብረት ስራ ማህበራት የገንዘብ ቁጠባና ብድር ዩኒየን የስራ ጊዜያቸዉን ያጠናቀቁ የቦርድ አመራሮችና በጠቅላላ ጉባኤ የተመረጡ አድስ የቦርድ አመራሮች በዛሬዉ እለት የስራ ርክክብ አደረጉ፡፡ በርክክብ ስነ ስርአት ላይም የስራ ጊዜአቸዉን ያጠናቀቁ አመራሮች አድስ ለተመረጡ አመራሮች ሀሳብና አስተያየት የሰጡ ሲሆን ከነዚህም ዉስጥ የዩኒየኑ ቁጥጥር ኮሚቴ የነበሩት አቶ ሀይሌ ተስፍየ እኛ በነበርንበት ዘመን አንድ አይነት አስተሳሰብና አመለካከት በመያዝ ከቅጥር ሰራተኞች ጋር ሁነን ዩኒየኑን የተሻለ ደረጃ ላይ እንድደርስ በማድረግ ተሸላሚ አድርገናል፡፡እናንተም አድስ አመራሮች ዪኒየኑን ከዚህ የበለጠ ደረጃና ጠንካራ ተቋም እንድሆን የተጣለባችሁን ሀላፊነት እንድትወጡ ትልቅ የቤት ስራ ሰጥተናችኀል ብለዋል፡፡ሌሎች የቦርድ አመራሮችም ከዩኒየኑ አመራርነት ብንለቅም ለአድስ አመራሮች ከጎናቸዉ በመሆን ድጋፍ እንደሚያደርጉላቸዉ ሀሳብ ሰተዋል፡፡ አድስ ከተመረጡ አመራሮችም ዉስጥ የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ዳዉድ ሙህየ የተሰጠንን የቤት ስራ ተቀብለን ህዝብ የጣለብንን ሀላፊነት በመወጣት ተቋሙን ዉጤታማ እናደርጋለን በማለት ሀሳብ በመስጠት የስራ ርክክብ አድርገዋል፡፡