Zemen Bank S.C.

Zemen Bank S.C. Whether you are working hard or out relaxing, We are at your service! Our Values include: Upholding the highest standards, being progressive and innovative.

Zemen Bank is a proudly Ethiopian, professional, dynamic, world-class and a totally customer financial institution. Our Personality is: To be challenging, spirited, provocative, ambitious and successful and to be friendly and courteous in all our relationships. To our Customers: We offer a professional partnership, trust and outstanding levels of service. Zemen Bank stands for innovation and excellence in everything we do.

‘’ የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪን መደገፉን አጠናክሮ ይቀጥላል’’አቶ ሚካኤል ፀጋዬ የዘመን ባንክ ቺፍ ሆልሴል ባንኪን ኦፊሰር አቶ ሚካኤል ፀጋዬ የኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘር...
06/05/2026

‘’ የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪን መደገፉን አጠናክሮ ይቀጥላል’’
አቶ ሚካኤል ፀጋዬ
የዘመን ባንክ ቺፍ ሆልሴል ባንኪን ኦፊሰር አቶ ሚካኤል ፀጋዬ የኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪን መደገፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለፁ፡፡ አቶ ሚካኤል ይህን የገለፁት በአዲስ አበባ በተካሄደው የአለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት ማህበር (አይኤቲኤ) የፎከስ አፍሪካ ኮንፈረንስ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው፡፡
አቶ ሚካኤል በኢትዮጵያ እየተሻሻለ የመጣውን የፋይናንስ ሁኔታና በቀጥታ ለአቪዬሽን ኢንዱስትሪ የሚሰጠውን ዘርፈ ብዙ ጥቅም በተመለከተ ማብራሪያ ያቀረቡ ሲሆን ሰኔ 2016 ዓ.ም የተጀመሩት ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚያዊ ማሻሻያዎች በገበያ ላይ የተመሠረተ የምንዛሬ ተመን ፣ ነፃ የውጭ ምንዛሪ ገበያ እና የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ መቋቋምን ጨምሮ ሌሎች የፖሊሲ ለውጦች የበለጠ ነፃ ገበያና ምቹ ኢንቨስትመንትን እንደሚፈጥሩ ተናግረዋል፡፡
አቶ ሚካኤል ጨምረውም ኢትዮጵያ ለሁሉም ክፍት ወደሆነ፣ ተወዳዳሪና ለተገበያዮች ምቹ ገበያ እየተሸጋገረች እንደሆነ ገልፀው የተሻሻለ የውጭ ምንዛሪ ተደራሽነት መኖሩ ለነዳጅ አቅርቦት ፣ ለኪራይና ለጥገና ክፍያዎች አየር መንገዶችን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን አፅንዖት ሰጥተዋል ።
"እነዚህ ማሻሻያዎች የኢኮኖሚ እድገትን በማጎልበት፣ ኤክስፖርትን በመደገፍ፣ ግልፅነትን በመፍጠር የባለሀብቶችን በራስ መተማመን ያሳድጋሉ" ያሉት አቶ ሚካኤል የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪን የበለጠ ለመደገፍ በጠንካራና በአስተማማኝ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ሁለገብ የባንክ አገልግሎት ለመስጠት የመጀመሪያው የሆነው ዘመን ባንክ፣ የአቪዬሽን ዘርፍን ጨምሮ ለኮርፖሬት ደንበኞች በላቀ የደንበኞች አገልግሎት ፣ በላቀ የቴክኖሎጂ ፈጠራ፣ በንግድ ፋይናንስ፣ በድንበር ተሻጋሪ የክፍያ አገልግሎቶችና ልዩ የግንኙነት ባንኪንግ መስጠቱን ቀጥሏል።
#ዘመንባንክ

ዘመን ባንክ ለዓለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት ማኅበር አጋርነቱን አሳየዓለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት ማኅበር (IATA) በአዲስ አበባ ባዘጋጀውና የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ ከተለያዩ...
30/04/2026

ዘመን ባንክ ለዓለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት ማኅበር አጋርነቱን አሳየ
ዓለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት ማኅበር (IATA) በአዲስ አበባ ባዘጋጀውና የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ ከተለያዩ አገራት የተወከሉ ተሳታፊዎች ለተገኙበት ኮንፈረንስ ዘመን ባንክ ግንባር ቀደም አጋርነትን አሳየ፡፡
የአፍሪካን አቪዬሽን ደህንነት፣ ተደራሽነትና ኦፕሬሽናል ብቃት ላይ በማተኮር የሚካሄደው ስብሰባ በስካይ ላይት ሆቴል ሚያዚያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በተከፈተበት ወቅት ወ/ሮ እንዬ ቢምር የዘመን ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ፣ አቶ አስራት ታደሰ የሪቴይል ባንኪንግ ቺፍ ኦፊሰርና አቶ ሚካኤል ፀጋዬ የኮርፖሬት ባንኪንግ ቺፍ ኦፊሰር በእንግድነት ተገኝተዋል፡፡ ከተለያዩ ተቋማት ተወካዮች ጋርም ውይይት አድርገዋል፡፡
#ዘመንባንክ

ለተከበራችሁ ደንበኞቻችን፤የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ አዲስ አበባንና ሐረሪ ክልልን ጨምሮ በ27 ዋና ዋና ከተሞች የሚገኙ የባንካችን ደንበኞች እስከ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም...
28/04/2026

ለተከበራችሁ ደንበኞቻችን፤
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ አዲስ አበባንና ሐረሪ ክልልን ጨምሮ በ27 ዋና ዋና ከተሞች የሚገኙ የባንካችን ደንበኞች እስከ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ሂሳባቸውን ከፋይዳ ቁጥር (ብሔራዊ መታወቂያ) ጋር ማስተሳሰር እንዳለባቸው አስገንዝቧል። በተጨማሪም በተቀሩት የሀገራችን ክፍሎች የሚገኙ ደንበኞች እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ማጠናቀቅ እንደሚኖርባቸው አስታውቋል፡፡
እርስዎም እስካሁን ድረስ የፋይዳ ቁጥርዎን ከዘመን ባንክ ሂሳብ ቁጥርዎ ጋር ካላስተሳሰሩ ከተጠቀሰው ቀን በፊት ካሉበት ሆነው ይህንን ማስፈንጠሪያ https://fayda.zemenbank.com/ በመጠቀም ወይም ወደሚቀርብዎት የዘመን ባንክ ቅርንጫፍ በመሄድ ሂሳብዎን ከፋይዳ ጋር እንዲያስተሳስሩ በአክብሮት እንጠይቅዎታለን። ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በ6500 ይደውሉልን፡፡
ስለ ትብብርዎ እናመሰግናለን።
ዘመን ባንክ፤
የላቀ አገልግሎት ማዕከል!
#ዘመንባንክ

ዘመን ባንክና የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚውል 40 ሚሊዮን ዩሮ ለማቅረብ ተስማሙዘመን ባንክና የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ - ግሎባል በአውሮፓ ህብረትና የኢት...
21/04/2026

ዘመን ባንክና የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚውል 40 ሚሊዮን ዩሮ ለማቅረብ ተስማሙ

ዘመን ባንክና የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ - ግሎባል በአውሮፓ ህብረትና የኢትዮጵያ ቢዝነስ ፎረም ወቅት በግብርና ለተሰማሩ ተቋማት የሚውል 40 ሚሊዮን ዩሮ ስምምነት ተፈራርመዋል።
በስምምነቱ መሰረት የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ 20 ሚሊዮን ዩሮ ለዘመን ባንክ የሚያቀርብ ሲሆን፣ ዘመን ባንክ በበኩሉ ተመሳሳይ መጠን ያለው ገንዘብ በኢትዮጵያ ብር ለተጠቃሚዎች ያቀርባል። ይህም ኢንቨስትመንት ባንኩ በኢትዮጵያ ውስጥ ለንግድ ባንክ በቀጥታ የሰጠው የመጀመሪያው ብድር በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል ።
ይህ የፋይናንስ ድጋፍ ዘመን ባንክ በኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ለተሰማሩና ምርቶቻቸውን ወደ ውጭ ለሚልኩ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ብድር ለማቅረብ ያስችለዋል፡፡ ከአጠቃላይ የገንዘብ ድጋፉ 30 በመቶ የሚሆነው የብድር መጠን የአየር ንብረትና የአካባቢ ጥበቃ ላይ ትኩረት ለሚያደርጉ የግብርና ሥራዎች ይመደባል፡፡ በተጨማሪም የስምምነቱ አንዱ አካል የሴቶችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በመሆኑ፤ ከበጀቱ ቢያንስ 30 በመቶ የሚሆነው በሴቶች ባለቤትነት ሥራ ላይ ላሉ፣ በሴቶች ለሚመሩ ወይም ለሴቶች የሥራ ዕድል ለሚፈጥሩና ምርትና አገልግሎት ላላቸው ድርጅቶች እንዲውል ተለይቷል።
ስምምነቱ ሚያዝያ 12 ቀን 2018 በአውሮፓ ህብረትና በኢትዮጵያ ቢዝነስ ፎረም ወቅት በአቶ አስራት ታደሰ የዘመን ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተወካይና የሪቴይል ባንኪንግ ቺፍ ኦፊሰር እና ሚስስ ሌይላ ትራኦሬ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ህብረት የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ተጠሪ መካከል ሚስተር ጆዜፍ ሲኬላ የአውሮፓ ዓለም አቀፍ የግንኙነቶች ሐላፊ በተገኙበት ተፈርሟል።

#ዘመንባንክ

ዘመን ባንክ በቀዳሚነት ፕሪምየም ማስተር ካርድ አቅራቢነቱ እውቅና ተሰጠውዘመን ባንክ ከ5 ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ፕሪምየም ማስተር ካርድ አቅራቢ በመሆን እየሰጠ ላለው አገልግ...
09/04/2026

ዘመን ባንክ በቀዳሚነት ፕሪምየም ማስተር ካርድ አቅራቢነቱ እውቅና ተሰጠው

ዘመን ባንክ ከ5 ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ፕሪምየም ማስተር ካርድ አቅራቢ በመሆን እየሰጠ ላለው አገልግሎት ከማስተር ካርድ እውቅና ተሰጠው፡፡
ሽልማቱን ሚ/ር ሼይራያር አሊ የማስተር ካርድ ምክትል ፕሬዝዳንትና የምስራቅ አፍሪካና የህንድ ውቅያኖስ ደሴቶች ሐላፊ ለአቶ ደረጀ ዘበነ የዘመን ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሚያዚያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም አስረክበዋል፡፡
በዚህ ወቅት ማስተር ካርድና ዘመን ባንክ ለዓመታት የዘለቀውን ስትራቴጂያዊ አጋርነታቸውን ይበልጥ አጠናክረው ለመቀጠል የሚያስችል ውይይት ካደረጉ በኋላ ይህን ለዓመታት የዘለቀ ግንኙነታቸውን ይበልጥ አጠናክሮ ለመቀጠል የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
#ዘመንባንክ

Address

Senga Tera Ras Abebe Aregay Street
Addis Ababa
1212

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zemen Bank S.C. posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Zemen Bank S.C.:

Share