Fancy Business consult ፋንሲ የንግድአማካሪ

Fancy Business consult ፋንሲ የንግድአማካሪ Financial and Business consultancy services

አዋሽ ባንክ ሦስት የዲጂታል ባንክ አገልግሎቶችን አስጀመረ  :  አቢሲኒያ ባንክና ቪዛ ካርድ ድንበር ተሻጋሪ ክፍያን ለማስፋፋት ተስማሙ አዋሽ ባንክ በስድስት ወሮች ብቻ በዲጂታል የክፍያ አማ...
18/03/2026

አዋሽ ባንክ ሦስት የዲጂታል ባንክ አገልግሎቶችን አስጀመረ

:
አቢሲኒያ ባንክና ቪዛ ካርድ ድንበር ተሻጋሪ ክፍያን ለማስፋፋት ተስማሙ

አዋሽ ባንክ በስድስት ወሮች ብቻ በዲጂታል የክፍያ አማራጮች ከአንድ ትሪሊዮን ብር በላይ ማንቀሳቀስ መቻሉንና ለሬሚታንስ የገንዘብ ዝውውር መተግበሪያ የሚሆን ፕላትፎርም ጨምሮ ሦስት የዲጂታል የባንክ አገልግሎቶችን ወደ ሥራ ማስገባቱን አስታወቀ፡፡ አቢሲኒያ ባንክ ደግሞ ከቪዛ ካርድ ጋር ስትራቴጂክ ያለው ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
አዋሽ ባንክ ባለፈው ሐሙስ ሦስቱን አዲስ የዲጂታል አገልግሎት ባስተዋወቀበት ፕሮግራም ላይ እንደገለጸው በደጂታል የባንክ አገልግሎት ዘርፍ እየታየ ያለው የገንዘብ እንቅስቃሴ በእጅጉ እየጨመረ ነው፡፡
የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሐይ ሽፈራው እንደገለጹት ባንኩ ባሉት የተለያዩ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች እየሰጠ ያለው አገልግሎት በእጅጉ እየጨመረ በመምጣቱ ከሐምሌ 2017 እስከ ታኅሳስ 2018 ዓ.ም. ባሉት በስድስት ወራት ብቻ ከአንድ ትሪሊዮን ብር በላይ መንቀሳቀስ ችሏል፡፡
ይህን ያህል መጠን ያለው እንቅስቃሴ ያደረገው ከዚህ ቀደም ተግባራዊ ያደረጋቸው የዲጂታል የባንክ አገልግሎቶች ከግለሰቦች አልፎ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማትን በማካተት የተለያዩ አገልግሎቶችን በዲጂታል የክፍያ ሥርዓት ውስጥ እንዲገቡ ማድረግ በመቻሉ ነው፡፡
በዲጂታል የክፍያ ሥርዓት አገልግሎት እየሰጠባቸው ካሉት መካከል የኤሌክትሪክና የውኃ ክፍያ፣ የትምህርት ቤት ክፍያ ዲጂታል የብድር አገልግሎቶችና የመሳሰሉት ተጠቃሽ ሆነዋል፡፡

የወጪ ማስረጃ ውድቅ ሲደረግ ተቀናሽ ስለሚደረግ ወጪ  የሂሳብ መዝገብ የሚይዝ ማንኛውም ግብር ከፋይ ያቀረበው የወጪ ማስረጃ በታክስ ባለስልጣኑ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ምክንያት ውድቅ ሲደረግ የ...
17/03/2026

የወጪ ማስረጃ ውድቅ ሲደረግ ተቀናሽ ስለሚደረግ ወጪ

የሂሳብ መዝገብ የሚይዝ ማንኛውም ግብር ከፋይ ያቀረበው የወጪ ማስረጃ በታክስ ባለስልጣኑ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ምክንያት ውድቅ ሲደረግ የሚከተሉት ሁኔታዎች ከተሟሉ ወጪው በከፊል ይያዝለታል፡-

👉 ወጪው ገቢን ለማመንጨት የወጣ ከሆነ
👉 ወጪው የድርጅቱን የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴ ለማስቀጠል ከሆነ
👉 ለድርጅቱ ህልውና ወይም ዋስትና ለመስጠት የወጣ ከሆነ

የሚፈቀደው የወጪ መጠን (የመቶኛ ቀመር)

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የወጪ ማስረጃውን ውድቅ ቢያደርገውም፣ ከላይ የተጠቀሱት ነጥቦች ከተረጋገጡ በገበያ ዋጋ ተሰልቶ ከታች ባለው መጣኔ መሰረት ወጪው ይያዝለታል፡-

👉 ለቋሚ ንብረት የገበያ ዋጋው ——— 70%
👉 ለሌሎች ዕቃዎች ወይም አገልግሎቶች የገበያ ዋጋው ——— 65%

ወጪው ሙሉ በሙሉ ውድቅ የሚደረግባቸው ሁኔታዎች

👉ወጪው ለድርጅቱ ስራ አስፈላጊ መሆኑ ካልተረጋገጠ።
👉የሀሰት ደረሰኝ (Illegal Receipt)፤ ምንም አይነት የንግድ ልውውጥ ሳይኖር የተቆረጠ ደረሰኝ ከሆነ።
👉 ህገ-ወጥ ደረሰኝ፤ በህግ እውቅና ከሌለው አካል የተገኘ ወይም የተጭበረበረ ሰነድ ከሆነ።

በታክስ ጉዳዮች ትምህርት ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ

Awash Bank Registers 54 Million Shares with Capital Market Authority Ahead of Planned ListingThe Ethiopian Capital Marke...
17/03/2026

Awash Bank Registers 54 Million Shares with Capital Market Authority Ahead of Planned Listing

The Ethiopian Capital Market Authority has approved the registration of more than 54 million existing ordinary shares of Awash Bank S.C., according to a public notice issued March 16, marking a significant regulatory milestone for Ethiopia's largest private bank as it advances toward a planned listing on the Ethiopian Securities Exchange.

The registration covers 54,066,089 shares already held by the bank's existing shareholders, formalized under Articles 4 and 29 of the Public Offer and Trading of Securities Directive No. 1030/2024. The directive requires all securities offered, sold, or previously issued to the public to be registered with the Authority unless specifically exempted, ensuring transparency and regulatory oversight as Ethiopia's capital market develops.

Awash Bank is among six commercial banks that have received "Approval in Principle" from the ESX to list on the Main Market, alongside Dashen Bank, Bank of Abyssinia, Abay Bank, Anbesa Bank, and Amhara Bank. Dashen Bank and Bank of Abyssinia have already completed securities registration and published prospectuses, positioning them closest to formal listing and public trading.

The ECMA emphasized that the notice is published solely to notify the public of the securities registration and shall not be construed as an endorsement or solicitation to buy or sell any securities.

Awash Bank, which dominates Ethiopia's retail and corporate banking sectors, is now fully compliant with ECMA rules for public disclosure and trading of its shares. The registration is seen as a key step as more financial institutions prepare to enter the formal securities market, potentially paving the way for future public offerings and secondary market trading.

ለአክሲዮን ፈላጊዎች በሙሉ የኢትዮጲያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ባፀደቀው የዳሸን ባንክ አ.ማ የደንበኛ ሳቢ መግለጫ መሰረት፤ አዲስ አክሲዮን ለመግዛት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን፣ በዋናው ...
18/02/2026

ለአክሲዮን ፈላጊዎች በሙሉ

የኢትዮጲያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ባፀደቀው የዳሸን ባንክ አ.ማ የደንበኛ ሳቢ መግለጫ መሰረት፤ አዲስ አክሲዮን ለመግዛት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን፣ በዋናው መስሪያ ቤት በመገኘት በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ፈቃድ በተሠጣቸው የአክሲዮን ደላሎች/ኢንቨስትመንት ባንኮች/ በኩል የግብይት ሂሳብ በመክፈት እስከ መጋቢት 07 ቀን 2018 ዓ.ም የአክሲዮን ግዢውን ማከናወን የምትችሉ መሆኑን በደስታ ይገልፃል፡፡

ማሳሰቢያ፡-ሁሉም ባለሃብቶች የዳሸን ባንክ ሙሉ ደንበኛ ሳቢ መግለጫን በሙሉ እንዲያነቡ ይበረታታሉ፤ ለውሳኔ የተቸገሩ ከሆነ በኢትዮጲያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ፍቃድከተሰጣቸው ገለልተኛ የፋይናንስ አማካሪዎች ምክር ይጠይቁ፣ የደንበኛ ሳቢ መግለጫው መጽደቅ ሰነደ ሙዓለ ነዋዮችን ባለሃብቶች እንዲገዙ የተሰጠ ምክር ወይም ድጋፍ ተደርጎ አይወሰድም፡፡ ይህ ማስታወቂያ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን (ECMA) ፈቃድ አግኝቷል፡፡

ለበለጠ መረጃ በአቅራቢያችሁ የሚገኙ የባንካችን ቅርንጫፎችን ይጎብኙ።

ባንኮች ለተመረጡ የገቢ ዕቃዎች የጉምሩክ ዋጋን እንደ አመላካች ዋጋ እንዲጠቀሙ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀባንኮች ለተመረጡ የገቢ ዕቃዎች የብድር ሰነድ (Letters of Credit) ...
25/01/2026

ባንኮች ለተመረጡ የገቢ ዕቃዎች የጉምሩክ ዋጋን እንደ አመላካች ዋጋ እንዲጠቀሙ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ

ባንኮች ለተመረጡ የገቢ ዕቃዎች የብድር ሰነድ (Letters of Credit) ይሁን ሌላ ክፍያ መንገድ ሲፈቅዱ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ተመንን እንደ አመላካች ዋጋ እንዲጠቀሙ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሐምሌ 2016 ዓ.ም ተግባራዊ ያደረገውን የውጭ ምንዛሪ መመሪያን ተከትሎ፣ የሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ተመን በገበያ እንዲወሰን መደረጉ ይታወቃል፡፡ መመሪያው ባንኮች ከደንበኞቻቸው ጋር በመደራደር የውጭ ምንዛሪ መሸጫና መግዣ ተመኖችን መወሰን እንዲችሉ ይፈቅዳል፡፡

በተጨማሪም ባንኮች ቀደም ሲል ይጠቀሙበት የነበረው ዝቅተኛ የገቢ ዕቃዎች ዋጋ መመሪያ (Minimum Price Directive) (በመሰረዙ፣ አሁን ግን በአዲሱ የውጭ ምንዛሪ መመሪያ መሠረት የገቢ የዕቃዎችን ዋጋ ትክክለኝነት የማረጋገጥ ኃላፊነት አለባቸው።

ይሁን እንጂ፣ ባንኮች ለብድር ሰነድ (Letters of Credit) የሚጠቀሙባቸው ዋጋዎች ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የማጣቀሻ ዋጋዎች ጋር ሲነፃፀሩ ከፍተኛ ልዩነት እንዳላቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባደረገው ክትትል አረጋግጧል፡፡

በመሆኑም የዋጋ ልዩነቶቹን ለማስተካከልና የዋጋ ማጣቀሻዎችን ለማጣጣም ሁሉም ባንኮች ከጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም (January 27, 2026) ጀምሮ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ተመንን እንደ አመላካች ዋጋ ይጠቀማሉ። ይህም በባንክ ሥርዓቱና በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መካከል ያለውን የዋጋ ልዩነት ለማስወገድና የውጭ ምንዛሪ መረጃዎችን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ያስችላል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ
ጥር 17 ቀን 2018 ዓ.ም

የአክሲዮን ሽያጭ ጥሪ ማስታወቂያ
02/01/2026

የአክሲዮን ሽያጭ ጥሪ ማስታወቂያ

የዘምዘም ባንክ አጠቃላይ ሀብት ወደ 19.5 ቢሊዮን ብር ሲያድግ፣ የተቀማጭ ገንዘቡም በ69% መጨመሩ ተገለፀበኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ሸሪዓን መሰረት ያደረገውን አገልግሎት በፈር ቀ...
14/12/2025

የዘምዘም ባንክ አጠቃላይ ሀብት ወደ 19.5 ቢሊዮን ብር ሲያድግ፣ የተቀማጭ ገንዘቡም በ69% መጨመሩ ተገለፀ

በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ሸሪዓን መሰረት ያደረገውን አገልግሎት በፈር ቀዳጅነት በማስጀመር የሚታወቀው ዘምዘም ባንክ፣ ከታክስ በፊት ከ1.23 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ በማስመዝገብ በታሪኩ ከፍተኛውን ደረጃ ላይ መድረሱን አስታውቋል፣

የተከፈለ ካፒታሉን ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ በማድረስ ብሔራዊ ባንክ ያስቀመጠውን የካፒታል ገደብ ከቀነ-ገደቡ አስቀድሞ በማሟላት፣ ለመጀመሪያ ጊዜ የትርፍ ክፍፍል (Dividend) ለመስጠት የሚያስችለውን ምዕራፍ መሻገሩን ጠቁሟል።

ዛሬ ታህሳስ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው 5ኛው መደበኛ እና 4ኛው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ በ2017 የበጀት ዓመት ታሪካዊ ስኬት ማስመዝገቡን የገለፀው ባንኩ አጠቃላይ ሀብቱ ወደ 19.5 ቢሊዮን ብር ያደገ ሲሆን፣ የተቀማጭ ገንዘቡም ካለፈው ዓመት የ69% ጭማሪ በማሳየት 13.5 ቢሊዮን ብር ደርሷል።

ባንኩ የቅርንጫፍ መስፋፋት በማድረግ እና የዋና መስሪያ ቤት ሕንፃ ግንባታ ዲዛይን በማጠናቀቅ፣ እንዲሁም አዲስ ገለልተኛ የቦርድ አባላትን ጨምሮ አዲስ አመራር በመምረጥ፣ በ2030 (እ.ኤ.አ) በአፍሪካ ቀዳሚ የሸሪዓ ባንክ የመሆን ራዕዩን ለማሳካት ቁርጠኝነቱን አረጋግጧል።

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በ2017 የበጀት ዓመት ከግብርና መጠባበቂያ በፊት ከ1.17 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ ማትረፍ መቻሉን አስታውቋል። ይህ ውጤት የተመዘገበው በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም ...
12/12/2025

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በ2017 የበጀት ዓመት ከግብርና መጠባበቂያ በፊት ከ1.17 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ ማትረፍ መቻሉን አስታውቋል። ይህ ውጤት የተመዘገበው በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢኮኖሚ ሁኔታው አለመረጋጋት በበዛበት ወቅት መሆኑን ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገልጸዋል።

ባንኩ በተጠናቀቀው ዓመት ከ5.56 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በማስመዝገብ የ37% ዕድገት ያሳየ ሲሆን፣ ጠቅላላ ሀብቱም ከ34.4 ቢሊዮን ብር በላይ በመድረስ የ42% ዕድገት ማሳየቱን ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።

እንደ ባንኩ ሪፖርት ከሆነ 7.53 ቢሊየን ብር ተቀማጭ ገንዘብ በመሰብሰብ የ41% ብልጫ በማሳየት አጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘቡን ወደ 25.75 ቢሊየን ብር አሳድጓል።

ይህን ውጤት ለማስመዝገብ የቻለው ለደንበኞች ከፍ ያለ አገልግሎት በመስጠት፣ የገበያውን ተለዋዋጭነት በመረዳትና ውጤታማ የሥራ አመራር በመዘርጋት እንዲሁም ንብረት በማሰባሰብ ጥረት በማድረግ መሆኑን ገልጿል።

የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር የማስተሳሰር ስራ በይፋ ተጀመረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፋይናንስ ዘርፉን ዲጂታል ለማድረግ ከብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጋር በመተባበር የባንክ...
10/12/2025

የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር የማስተሳሰር ስራ በይፋ ተጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፋይናንስ ዘርፉን ዲጂታል ለማድረግ ከብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጋር በመተባበር የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር የማጣመር ስራ በይፋ ማስጀመሩን አስታውቋል።

ሆኖም ሁሉም የባንክ ደንበኞች ያላቸውን የባንክ ሂሳብ ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያቸው ጋር ማስተሳሰር ይጠበቅባቸዋል ተብሏል።

ደንበኞች ይህንን ሂደት እስከ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ማጠናቀቅ እንዳለባቸውም ተገልጿል።

09/12/2025

በ2018/2025 ግብር ዓመት በየ3 ወሩ የሚከፈለዉ ቅድመ ግብር የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ተደርጓል

| በገቢ ግብር አዋጅ ማሻሻያ መሰረት ከተያዘዉ የግብር አመት በፊት በነበረዉ የግብር አመት የተከፈለዉን ግብር 25 በመቶ እንደሚከፈል መደንገጉ ይታወቃል።

በማሻሻያ አዋጁ መሰረት ገቢዎች ሚኒስቴር የ2018/2026 ግብር አመት ዓመታዊ የትርፍ ግብር በየሩብ አመቱ (በየሦስት ወሩ) በማሳወቅ የሚከፈልበት የጊዜ ሰሌዳ አሳውቋል፡፡

በእዚህም መሰረት በኢትዮጵያ የጊዜ ቀመር ለሚጠቀሙ (ሒሳባቸዉን ሰኔ 30 ለሚዘጉ) ግብር ከፋዮች:-

• የመጀመሪያዉ ሩብ አመት የመክፈያ ጊዜ ከየካቲት 1 እስከ የካቲት 30 ፣ ከሀምሌ 1- መስከረም 30 የተቀነሰ 3 % ቅድመ ግብር (withholding) በዚህ ወር ከሚከፈለዉ ክፍያ ላይ ተቀናሽ ይደረጋል።

• የሁለተኛ ሩብ አመት የመክፈያ ጊዜ ከግንቦት 1 አስከ ግንቦት 30 ፣ከጥቅምት 1 እስከ ታህሳስ 30 የተቀነሰ 3 በመቶ ቅድመ ግብር (withholding) በዚህ ወር ከሚከፈለዉ ክፍያ ላይ ተቀናሽ ይደረጋል

• የሦስተኛዉ ሩብ አመት የመክፈያ ጊዜ ከነሀሴ 1 እስከ ነሀሴ 30 ፣ከጥር 1 እስከ መጋቢት 30 የተቀነሰ 3 % ቅድመ ግብር (withholding) በዚህ ወር ከሚከፈለዉ ክፍያ ላይ ተቀናሽ ይደረጋል።

በ2019 ከሀምሌ 1 እስከ ጥቅምት 30 አጠቃላይ የ2018 ግብር አመት የትርፍ ግብር ቀድመዉ የከፈሉትን በመቀነስ ቀሪዉን ይከፍላሉ፣ በትርፍ የተከፈለም ካለ ተመላሽ ይጠይቃሉ።

በግሪጎሪያን የጊዜ ቀመር ለሚጠቀሙ (ሒሳባቸዉን ዲሴንበር 30 ለሚዘጉ) ግብር ከፋዮች ፦

• የመጀመሪያዉን ሩብ አመት የመክፈያ ጊዜ August 1 እስከ August 30 ፣ January 1 እስከ March 30 የተቀነሰ 3 % ቅድመ ግብር (withholding) በዚህ ወር ከሚከፈለዉ ክፍያ ላይ ተቀናሽ ይደረጋል።

• የሁለተኛ ሩብ አመት የመክፈያ ጊዜ November 1 እስከ November 30 ፣ከApril1 እስከ June 30 የተቀነሰ 3 % ቅድመ ግብር (withholding) በዚህ ወር ከሚከፈለዉ ክፍያ ላይ ተቀናሽ ይደረጋል።

በ2026 January 1 እስከ April 30 አጠቃላይ የ2025 ግብር አመት የትርፍ ግብር ቀድመዉ የከፈሉትን በመቀነስ ቀሪዉን ይከፍላሉ፣በትርፍ የተከፈለም ካለ ተመላሽ የሚጠይቁ መሆኑን ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ያወጣው መርሃ ግብር ያሳያል።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251911863248

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Fancy Business consult ፋንሲ የንግድአማካሪ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Fancy Business consult ፋንሲ የንግድአማካሪ:

Share