Sunni

Sunni Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Sunni, Financial service, Addis Ababa.

24/09/2018

ሰቆቃው ጴጥሮስ
• • •
ከጴጥሮስ– ያቺን ሰዓት ቴአትር
✍✍✍✍✍

አዬ፥ ምነው እመ ብርሃን? ኢትዮጵያን ጨከንሽባት?
ምነው ቀኝሽን ረሳሻት?
እስከመቼ ድረስ እንዲህ፥ መቀነትሽን ታጠብቂባት?
ልቦናሽን ታዞሪባት?
ፈተናዋን፥ ሰቀቀንዋን፥ ጣሯን ይበቃል ሳትያት?
አላንቺ እኮ ማንም የላት….
አውሮጳ እንደሁ ትናጋዋን፥ በፋሽታዊ ነቀርሳ
ታርሳ፥ ተምሳ፥ በስብሳ
ሂትለራዊ እባጭ ጫንቃዋን፥ እንደኰረብታ ተጭኗት
ቀና ብላ እውነት እንዳታይ፥ አንገቷን ቁልቁል ጠምዝዟት
ነፍሷን ድጦ ያስበረከካት
ሥልጡን፥ ብኩን፥ መፃጉዕ ናት፤…
እና ፈርቼ እንዳልባክን፥ ሲርቀኝ የኃይልሽ ውጋገን
አንቺ ካጠገቤ አትራቂ፥ በርታ በይኝ እመ ብርሃን
ቃል ኪዳኔን እንዳልረሳት፥ እንዳልዘነጋት ኢትዮጵያን።
አዎን፥ ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እሸሸግበት ጥግ አጣሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ፥
እማማ ኢትዮጵያን መንፈሴ፥ ተፈትቶ እንዳይከዳት ሠጋሁ…
አዋጅ፥ የምሥራች ብዬ፥ የትብት ምግቤን ገድፌ
ከናቴ ማኅፀን አልፌ
በኢትዮጵያ ማኅፀን አርፌ
ከአፈርዋ አጥንቴን ቀፍፌ
ደሜን ከደሟ አጠንፍፌ
ከወዟ ወዜን ቀፍፌ
በሕፃን እግሬ ድሄባት፥ በሕልም አክናፌ ከንፌ
እረኝነቴን በሰብሏ፥ በምድሯ ላብ አሳልፌ
ከጫጩትና ከጥጃ፥ ከግልገል ጋር ተቃቅፌ፤
በጋው የእረኛ አደባባይ፥ ክረምት እንደወንዙ ፍሳሽ
የገጠር የደመና ዳስ፥ በገደል ሸለቆ አዳራሽ
ከቆቅና ከሚዳቋ፥ ከዥግራ ጠረን ስተሻሽ
በወንዝ አፋፍ ሐረግ ዝላይ፥ መወርወር መንጠልጠል ጢሎሽ
ከፍልፈል ጋር ሩጫ ስንገጥም፥ ከቀበሮ ድብብቆሽ
ከናዳ ጫፍ ሣር አጨዳ፥ ለግት ላሜ ትንሽ ግጦሽ
ለጥጃዬ የሌት ግርዶሽ
ለጥማድ በሬዎች ራት፥ ለማታቸው ትንሽ ድርቆሽ፥
ለግልገሌ ካውሬ ከለል
እማሣው ሥር ጐጆ መትከል
ለፀሐይ የሾላ ጠለል፥ለዝናብ የገሳ ጠለል
ውሎ የንብ ቀፎ ማሰስ፥ያበባ እምቡጥ ሲፈነዳ
የግጦሽ ሣር ሲለመልም፥ሲሰማሩ ሰደድ ሜዳ
አዝመራው ጣል ከንበል ሲል፥ከብቱ ለሆራ ሲነዳ
ፈረስ ግልቢያ ስሸመጥጥ፥ከወፎች ዜማ ስቀዳ
ልቤ በንፋስ ተንሳፎ፥በዋሽንት ዋይታ ሲከዳ....
ያቺን ነው ኢትዮጵያ የምላት
እመ ብርሃን እረሳሻት?
ያቺን የልጅነት ምስራች? የሕፃንነት ብሥራት
የሣቅ የፍንደቃ ዘመን፥ የምኞትየተስፋ ብፅአት
ያቺን የልጅነት እናት?
አዛኚቱ እንዴት ብለሽ፥ጥርሶችሽን ትነክሽባት?
•••

ስሜን በስምሽ ሰይሜ፥ባገልግሎትሽ ስዋትት
ከዜማ ቤት እቅኔ ቤት፥ከድጓ ቤት እመጻሕፍት፥
ካንቺ ተቆራኝታ ዕድሌ፥ካንቺ ተቆራኝታ ነፍሴ
ከቀፈፋ ደጀሰላም፥ከቤተልሔም ቅዳሴ
አኰ፥ቀፎ ፥ዳባ ለብሶ
ቅኔ ዘርፎ ግሥ ገሦ
መቅደስ አጥኖ፥ ማኅሌት ቆሞ
በልብስ ተክህኖ አጊጦ፥ በብር አክሊል ተሸልሞ
እመ ብርሃን ያንቺ ጽላት፥ነፍሴ ላይ በሳት ታትሞ
የመናኒው ያባ ተድላ፥ረድ ሆኜ አብሮኝ ታድሞ
ሕይወቴ እምነትሽን ጸንሶ
ሥጋ ፈቃዴ ተድሶ
ለሕንፃሽ መዲና ቆሞ፥ ለክብርሽ ድባብ ምሰሶ፤
ስሜን በስምሽ ሰይሜ፥ ሆነሽኝ የእምነቴ ፋኖስ
በዋዜማሽ ግሸን ማርያም፥ለክብርሽ ደብረ ሊባኖስ
ስሮጥ፥በወንበሩ አኖርሺኝ፥ በአንበሳው በቅዱስ ማርቆስ፤
ታዲያን ዛሬ ኢትዮጵያ ስትወድቅ፥ ከምትሰጪኝ ለፍርሃት ጦስ
ምነው በረኝነት ዕድሜ፥ ዓይኔን በጓጐጣት የሎስ
የጋኔል ጥንብ አንሳ ከንፎ፥ ወርዶ በጭለማ በርኖስ።
ባክሽ እመ ብርሃን ይብቃሽ፥ ባክሽ ምስለ ፍቁር ወልዳ
ጽናት ስጪኝ እንድካፈል፥ የእናቴን የኢትዮጵያን ፍዳ፤
ከነከሳት መርዝ እንድቀምስ፥ ከነደደችበት እቶን
የሷን ሞት እኔ እንድሞታት፥ገላዋ ገላዬ እንዲሆን።…
አዎን ፥ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እፀናበት ልብ አጣሁ።…
••••

ሕፃን ሆኜ የእርግብ ጫጩት፥አንዳንዴ ራብ ሲያዳክማት
ችጋር ከጐጆዋ ገፍቶ፥ እዛፍ ግርጌ ሲጥላት
እናቷ በርራ ደርሳላት
በአክናፏ ሙቀት ታቅፋት
እፍ እያለች ግንባሯ ላይ፥ሕይወት ስትነፍስባት
ወዲያው ነፍስ ትዘራለች
ሽር -ብር-ትር እያለች።
ባክሽ አንቺም አትራቂብኝ
እመ ብርሃን እናቴ፥ትንፋሽሽን እፍ በዪብኝ
ፅናትሽን እፍ በዪብኝ፥
ወይም ይቺን የሞት ጽዋ፥ ጥላዋ ነፍሴን ካፈናት
እንዳልጠጣት አሳልፊያት
መራራ ክንፏን ገንጥለሽ፥ቀጠሮ፥ ቃልዋን ግደፊያት፤....
አለዚያም ጽናትሽን ስጪኝ፥ልጠጣው ኪዳነ-ውሉን
የኔ ፈቃድ እምነትሽ ነው፥ያንቺ ፈቃድ ብቻ ይሁን።
እንደ ጳውሎስ እንድጸና፥ በፍርሃት እንዳልታሰር
በውስጤ ከሚታገለኝ፥ በሥጋ አውሬ እንዳልታወር
ለየዕለቱ ሞት እንዳልሰንፍ
የኪዳኔ ቃል እንዳይነጥፍ
ቃልሽ በሕሊናዬ ዲብ ፥ ኃይልሽ በሕዋሴ ይረፍ።
ፍርሃት ቢያረብብኝም፥ አንቺ ካለሺኝ አልሰጋም
ኩርምት ብዬ እችልበት፥ እሸሸግበት አይጠፋም
የግማደ መስቀሌን ጉጥ፥ እታገስበት አላጣም፥
አለዚያማ ብቻዬን ነኝ፥ ኢትዮጵያም አላንቺ የላት
አንቺ አፅኝኝ እንድጸናላት።
አስርጪብኝ የእምነት ቀንጃ፥ ለሥጋቴ አጣማጅ አቻ
ለጭንቀቴ– መቀነቻ።..。
አዎን፥ ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እሸሸግበት ጥግ አጣሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ…
✍✍✍✍✍
እሳት ወይ አበባ
(ከሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን)

17/07/2018

// //
🌻በአንድ ወቅት አንድ ፈጣሪ በሰጠው ጸጋ አመስግኖ የማያውቅ ስስታም ነጋዴ ነበር። ከዕለታት አንድ ቀን ለንግድ ስራ ከሄደበት ወደ ቤቱ ሲመለስ 100 የወርቅ ሳንቲም ይጠፋበታል።
ነጋዴው "100 የወርቅ ሳንቲም ያገኘ ካለ ወረታው ከፋይ
ነኝ" እያለ ቢለፈልፍም ሊያገኘው አልቻለም። አንድ ቀን ተስፋ ቆርጦ እቤት ቁጭ ብሎ እያለ አንድ ልብሱ የቆሸሸ ገጽታው የተጎሳቀለ ሰውዬ የነጋዴውን ቤት አንኳኳ።
በር ተከፍቶ ወደ ሳሎን ቤቱ ሲዘልቀ እንግዳው ሰውዬ የመጣበትን ጉዳይ እንዲህ ሲል አስረዳ ፦
ጌታዬ 100 የወርቅ ሳንቲም መንገድ ላይ
አግኝቼ ነበር። ባለቤቱም እርሶ እንደሆኑ ነው የተነገረኝ። ምንም የዕለት ጉርሻ የሌለኝ ድሀ ብሆንም የሰው ንብረት አልመኝም። ስለሆነም የወርቅ ሳንቲሞን ይዤሎት መጥቻለሁ አለ።
🌻የሚሰጠውን ጉርሻ ምን ሊሆን እንደሚችል በልቡ እያሰበ።
ነጋዴው ይህን ሲሰማ ወረታውን ላለመክፈል በአንዴ ፊቱ ተለዋወጠ። አንተ እንዳልከው 100 የወርቅ ሳንቲም ብቻ አይደለም የጠፈብኝ። በአጠቃላይ የጠፋብኝ የወርቅ ሳንቲም መጠን 125 ነው። ስለዚህ 25 የወርቅ ሳንቲም አስቀርተክብኛል። አሁን ሌላ ጣጣ ሳይከተልህ 25ቱን ሳንቲም መልስልኝ ሲል አስፈራራው።
ምስኪኑ ሰውዬ ከቅንነት ተነስቶ ያደረገው ነገር ያላሰበው ጣጣ ስለመጣበት እጅግ ተጨነቀ። "ጌታዬ እኔ ያገኘሁት ይሄ ብቻ ነው ምናልባት ሌላ ቦታ ወድቆ እንዳይሆን። በፈጣሪ እምልሎታለው እኔ አልወሰድኩም። በማለት ሊያስረዳው ሞከረ።
ይሁን እንጂ ሀብታሙ ነጋዴ አእምሮ በጥቅም ታውሮ ምንም አይነት የርህራሄ ስሜት ሊያሳይ አልቻለም በዚህም 25 የወርቅ ሳንቲም ወስዶብኛል በሚል ከሰሰው። ድሀው ሰውዬ ከዳኛ ፊት ቀርቦ እንዲህ ሲል ተከራከረ።
ክቡር ዳኛ ከ 100 የወርቅ ሳንቲም ውጪ ሌላ ነገር አላገኘሁም። አግኝቷል የሚል ምስክር። ከተገኘ ግን የሚሰጠኝን ቅጣት በጸጋ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ ሲል ተናገረ።
በዚህ ጊዜ ጉዳዩን ይመለከት የነበሩት ዳኛ ጠፋ የተባለው የወርቅ ሳንቲም መጠን ምን ያህል እንደሆነ ቀደም ብሎ መረጃ ደርሷቸው ስለነበር የሚከተለው ውሳኔ አስተላለፉ።
>>>>>>>
"ጠፋ የተባለው የወርቅ ሳንቲም 100 ብቻ እንደሆነ መረጃ አለን። እርስዎ የተከበሩ ከሳሽ ጠፋብኝ እያሉ ያሉት ደግሞ 125 ነው።
ስለዚህ 100 ው የወርቅ ሳንቲም የእርስዎ ሊሆን አይችልም። ምናልባት 125 የወርቅ ሳንቲም የወሰደ ሰው እስኪገኝ ድረስ ይጠብቁ።
አሁን የተገኘው ሳንቲም ግን ትክክለኛ ባለቤቱ እስካልተገኘ ድረስ ላገኘው ሰው እንዲሰጥ ወስንናል።"
የሚል ፍርድ ሰጡ በመጨረሻም ድሀው ሰውዬ ሀብት በሀብት ሆኖ ሲመለስ ስግብግቡ ነጋዴ ደግሞ ባዶ እጁን ለመመለስ ተገደደ።
መልካምነት ለራስ ነው። መልሶ ይከፍላልና!
ኢትዮጲያዊነት መልካምነት ነው።

23/04/2017

"የድንግል ፍሬ, የቤተልሄም ሕጻን, የግብጽ ስደተኛ, የቆሮንጦስ ባሕታዊ የቀራንዮ በግ, የትንሳኤ ብርሃን, ለኛ ብሎ ሞተ እናም ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ!!!"
መልካም ዳግማይ ትንሳኤ በዓል ይሁንላችሁ::

01/03/2017

ምኒልክ ሆይ! . . . የሰው ልጅ ለመኖር ሶስት መሠረታዊ ነገር ያስፈልጉታል::
ምግብ ፣ መጠለያና ልብስ ። እርሶ አራተኛ ነገር ሰጡን ክብር!
አመሰግንዎታለሁ!
የብልህነትዎን ፣ የአገር ፍቅርዎን ፣ የህዝብን ሀያልነት በአድዋ ገመድ ገምደውና ቋጥረው አሳይተውናል!
ምኒልክ ሆይ እምዬ መባል ሲያንስብዎ እንጂ አይበዛብዎም!
የልጅን ህመም ከእናት በላይ ማን ይረዳውና?!
ታመን እንዳንቀር መድሀኒት ፤ ጎላ ብለን እንድንታይ ብርሃን ፤ ለከፍታችን ደግሞ ሰገነት ሆነውናልና እጅ ነሳዎት!

02/03/2016

Dear Friends to day is the day that we celebrat the 120th Victory of Adwa. As History told us at the time the patriot of Ethiopia together with st. Giorgis help got victory agenst the great fashisht Itali and it become the sign of freedom for African also the stablishiment of pan-Africanizim movement.....................................

29/09/2015

Is there anyone who want 2B finantial intermideter 2 the vary first time in Ethiopia play a Gr8 role in secomdery market?

20/09/2015

Anybady in the group having business idea and willing to share it with the group is wellcome. U can inbox me the idea & we will deal 2gether on it. "BEGARA SERTEN BE HIBRET ENIDEGI"

18/09/2015

Laddis & Gentelman First of all i wolud like to say wellcome to my new page. This page is designed to make me & my firend's to share knowlege,skill & exprians also collaboratily to create some business plan that can generate good profit.

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sunni posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share