ENAT BANK S.C.

ENAT BANK S.C. Enat Bank S.C. is a Private Commercial Bank in Ethiopia.

We provide free financial education in our local communities and supplying our customers with the resources and answers they need to support their financial live. Enat Bank Face book page is dedicated to providing a place for people to connect and share about the positive things.

የሐዘን መግለጫየእናት ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ፣ የሥራ አመራር አባላትና ሠራተኞች በእማሆይ ፅጌ ማርያም ገብሩ   ህልፈተ ህይወት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ...
28/03/2023

የሐዘን መግለጫ
የእናት ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ፣ የሥራ አመራር አባላትና ሠራተኞች በእማሆይ ፅጌ ማርያም ገብሩ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመድና ለመላው ኢትዮጵያውያን መጽናናትን እንመኛለን።
ቀዳሚ የኢትዮጲያዊ የቫዬሊን እና ፒያኖ አቀናባሪ እማሆይ ፅጌ ማርያም የኢትዮጵያ ክላሲካል ሙዚቃዎች እናት ተብለው ይጠሩ ነበር ፡፡ ባንካችን እማሆይ ፅጌ ማርያም ገብሩ ለማህበረሰቡ ያደረጉትን አሰተዋጽኦ ግምት ውስጥ በማስገባት አዲስ አበባ ሀይሌ ጋርመንት አካባቢ የሚገኘውን ቅርንጫፋችንን በስማቸው መሰየማችን የሚታወስ ነው።
ማን እንደ እናት!

እናት ባንክ ዶ/ር ተዋበች ቢሻው ጎፋ ገብርኤል ቅርንጫፍ ተመርቆ ተከፈተ!---------------------------------------እናት ባንክ ወደ ውድ ደንበኞቹ መቅረቡን  በመቀጠል በአ...
25/03/2023

እናት ባንክ ዶ/ር ተዋበች ቢሻው ጎፋ ገብርኤል ቅርንጫፍ ተመርቆ ተከፈተ!
---------------------------------------
እናት ባንክ ወደ ውድ ደንበኞቹ መቅረቡን በመቀጠል በአዲስ አበባ ከተማ ጎፋ ገብርኤል አካባቢ ቅርንጫፍ በድምቀት ተመርቆ ተከፈተ:: እናት ባንክ የተመሰረተበትን የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ አቅም ማጎልበትንና ሁለንተናዊ የሴቶች ተጠቃሚነት የማረጋገጥ አስፈላጊነት ለማህበረሰቡ ለማስታወስ ባንካችን አዲሰ የከፈተውን ቅርንጫፍ የሴቶች መብት መታሰቢያ በሆነው ማርች ወር ተመርቆ ሊከፈት ችሏል።በምረቃው ሥነ ስርዓት ላይ ዶ/ር ተዋበች ቢሻው ጨምሮ ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የባንኩ የቦርድና የሥራ አመራር አባላት በተገኙበት ዛሬ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም በድምቀት ተመርቆ የተሟላ የባንክ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡ ባንኩ በመላው ሀገሪቱ 134 ቅርንጫፎች አሉት፡፡
ማን እንደ እናት!

ትርታ 97.6 ኤፍኤም እና እናት ባንክ በጋራ አብሮ ለመሥራት የአጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ። መጋቢት 13 ቀን 2015 ዓ.ም. በትርታ 97.6 ኤፍኤም  በተካሄደው ሥነ ሥርዓት የእናት ባንክ ...
23/03/2023

ትርታ 97.6 ኤፍኤም እና እናት ባንክ በጋራ አብሮ ለመሥራት የአጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ።
መጋቢት 13 ቀን 2015 ዓ.ም. በትርታ 97.6 ኤፍኤም በተካሄደው ሥነ ሥርዓት የእናት ባንክ የኦፕሬሽንስ ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ትዕግስት አባተ እና የትርታ ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዘካሪያስ ስንታየሁ አብሮ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የስምምነት ፊርማ ተፈራርመዋል::
በዕለቱም የጣቢያው እና የባንኩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገኝተዋል::
ትርታ 97.6 ኤፍኤም በሕትመት ሚዲያ ብሎም በብሮድካስት ሚዲያው የረጅም ዓመት ልምድ ባላቸው ሰባት ጋዜጠኞች ዘካሪያስ ስንታየሁ፣ ደረጄ ጠገናው፣ ብሩህይሁን በላይ፣ ግርማቸው እንየው፣ ሶፎንያስ እንየው፣ ውብሸት አሰፋ እና የኋላሸት ዘሪሁን እንዲሁም በታዋቂዋ ሥራ ፈጣሪ እና የሃይብሪድ ዲዛይን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር (ራይድ) መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ሳምራዊት ፍቅሩ አማካኝት ሐምሌ 3 ቀን 2012 ዓ.ም. ከመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የሥርጭት ፍቃድ አግኝቶ ሐምሌ 2 ቀን 2014 ዓ.ም. የሙከራ ሥርጭቱን እንደ ጀመረ ይታወቃል።
ከዚህ ቀደም ትርታ 97.6 ኤፍኤም ለሥርጭት እንዲበቃ እና እውን እንዲሆን የእናት ባንክ ከፍተኛ የገንዘብ እገዛ ማድረጉን የገለጹት አቶ ዘካሪያስ፣ የተፈጸመው ስምምነት የሁለቱን ተቋማት ትብብር የበለጠ እንደሚያጠናክረው ተናግረዋል። በሌላ በኩል ሚዲያውን መደገፍ ራሳችንን መደገፍ ነው ያሉት ወ/ሮ ትዕግስት፣ ትርታ 97.6 ኤፍኤም ብቁ ዜጎችን በማፍራትና አገርን በበጎ መልኩ በመገንባት ረገድ የበኩሉን አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።

ክብርት ሚኒስቴር እንኳን ደስ አልዎት!የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤናው ዘርፍ ላበረከቱት ከፍተኛ የመሪነት አስተዋፅዖ ከአምሪፍ ጤና አፍሪካ “Women in the Global ...
10/03/2023

ክብርት ሚኒስቴር እንኳን ደስ አልዎት!
የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤናው ዘርፍ ላበረከቱት ከፍተኛ የመሪነት አስተዋፅዖ ከአምሪፍ ጤና አፍሪካ “Women in the Global Word Award AHAIC2023” ስላገኙት እውቅና እንኳን ደስ አልዎት ለማለት እንወዳለን!

ዓለም  አቀፍ ሴቶች ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከበረ !የእናት ባንክ ከፍተኛ የስራ አመራሮች እና ሰራተኞች የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በደመቀ ሁኔታ በዋናው መስሪያ አክብረዋል፡፡ በዝግጅቱ ላይ የ...
09/03/2023

ዓለም አቀፍ ሴቶች ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከበረ !
የእናት ባንክ ከፍተኛ የስራ አመራሮች እና ሰራተኞች የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በደመቀ ሁኔታ በዋናው መስሪያ አክብረዋል፡፡
በዝግጅቱ ላይ የእናት ባንክ ኮርፖሬት ምክትል ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ገነት ሀጎስ እና ምክትል ፕሬዝዳንት ኦፕሬሽንስ ወ/ሮ ትግስት አባተ ተግኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን እናት ባንክ በ11 ባለራዕይ ሴቶች ተመስርቶ ላለፉት 10 ዓመታት ሁሉንም ማህበረሰብ ያማከለ በተለይም የሴቶችን አቅም በማጎልበት ላይ ትኩረት በማድረግ በውጤታማነት የተሟላ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ባንክ ነው፡፡
ማን እንደ እናት!

እንኳን ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን አደረሳችሁ!
08/03/2023

እንኳን ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን አደረሳችሁ!

እንኳን ለኢትዮጵያውያን የድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ !
01/03/2023

እንኳን ለኢትዮጵያውያን የድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ !

እናት ባንክ ከሰረገላ  ኃ/የተ/የግ/ማ  በጋር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ። ስምምነቱ  ሰረገላ ገበያ(SeregelaGebeya.com) የኤሌክትሮኒክስ ንግድ ሽያጭ እና ማከፋፈያ ፕ...
25/02/2023

እናት ባንክ ከሰረገላ ኃ/የተ/የግ/ማ በጋር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ። ስምምነቱ ሰረገላ ገበያ(SeregelaGebeya.com) የኤሌክትሮኒክስ ንግድ ሽያጭ እና ማከፋፈያ ፕላትፎርም መሰረት የተለያዩ የቤት ውስጥ አስቤዛ እና የንፅህና መጠበቂያ ምርቶች አቅርቦትና ሎጅስቲክስ ላይ የተሟላ የደንበኛ አገልግሎት በመስጠት የኢ-ክፍያና ኦን ላየን ግብይት
በሰረገላ ኢኮሜርስ ፕላት ፎርም (SeregelaGebeya.com Ecommerce) ከባንኩ ጋር በትብብር አብሮ ለመስራት ዓላማ ያደረገ ነው።
የመግባቢያ ስምምነቱን የእናት ባንክ ፕሬዚደንት አቶ ኤርምያስ አንዳርጌ በተገኙበት በባንኩ በኩል ወ/ሮ ገነት ሃጎስ የባንኩ የኮርፖሬት ሰርቪስ ም/ፕሬዚደንት በሰረገላ ኃ/የተ/የግ/ማ በኩል የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ኤልያስ ነጋሽ ዛሬ የካቲት 18, 2015 ዓ.ም በእናት ባንክ ዋና መስሪያ ቤት ተፈራርመዋል፡፡

ማን እንደ እናት!

ወደ ቅርንጫፎቻችን ይምጡ !በተመረጡ ቅርንጫፎቻችን ከኢትዮ ሰርከስ ኢንተርቴይመንት ቡድን ጋር በጋራ በመሆን በሰርከስ ትርዒት የታጀበ ስላንቺ ልዩ የቁጠባ ሂሳብ (ከፍተኛ የወለድ ምጣኔና ልዩ ...
23/02/2023

ወደ ቅርንጫፎቻችን ይምጡ !
በተመረጡ ቅርንጫፎቻችን ከኢትዮ ሰርከስ ኢንተርቴይመንት ቡድን ጋር በጋራ በመሆን በሰርከስ ትርዒት የታጀበ ስላንቺ ልዩ የቁጠባ ሂሳብ (ከፍተኛ የወለድ ምጣኔና ልዩ የብድር አገልግሎት የሚያስገኝ ) በስፋት የማስተዋወቅ ካምፔን በስምንቱ ቅርንጫፎቻችን በደመቀ ሁኔታ እንደተካሄደ ይታወሳል፡፡
ከሰኞ ቀን የካቲት 20,2015 ዓ.ም ጀምሮ በሚቀጥለው ሳምንት ስላንቺን በልዩ መልኩ የማስተዋወቅ ዘመቻ ስለሚካሄድ በዘሚ የኑስ ፊጋ ፣ሎሬት ሲስተር ጥበበ ማኮ ሰሚት፣ ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ ላፍቶ እና ፀሀይ ይትባረክ ለቡ ቅርጫፎቻችን እንድትታደሙ ስንጋብዝ በአክብሮት ነው፡፡
ማን እንደ እናት!

ጨንፈር ዓዲ-ግራት ቅርንጫፍ በድጋሚ  አገልግሎት መስጠት ጀመረ!እናት ባንክ ከዚህ ቀደም ተቋርጦ የነበረውን ጨንፈር ዓዲ-ግራት ቅርንጫፍ አገልግሎት በድጋሚ በመክፈት አገልግሎት መስጠት መጀመራ...
17/02/2023

ጨንፈር ዓዲ-ግራት ቅርንጫፍ በድጋሚ አገልግሎት መስጠት ጀመረ!
እናት ባንክ ከዚህ ቀደም ተቋርጦ የነበረውን ጨንፈር ዓዲ-ግራት ቅርንጫፍ አገልግሎት በድጋሚ በመክፈት አገልግሎት መስጠት መጀመራችን ስናበስራቹ ከፍተኛ ደስታ ይሰማናል፡፡ እንደዚህ ቀደሙ በባንካችን ቀልጣፋ አገልግሎት ደስተኛ እንደምትሆኑ በመተማመን ነው፡፡
ማን እንደ እናት!

ሁላችሁም ተጋብዛችኋል !!!እናት ባንክ ከኢትዮ ሰርከስ ኢንተርቴይመንት ቡድን ጋር በጋራ በመሆን የስላንቺን ልዩ የቁጠባ ሂሳብ (ከፍተኛ የወለድ ምጣኔና ልዩ የብድር አገልግሎት የሚያስገኝ ) ...
02/02/2023

ሁላችሁም ተጋብዛችኋል !!!

እናት ባንክ ከኢትዮ ሰርከስ ኢንተርቴይመንት ቡድን ጋር በጋራ በመሆን የስላንቺን ልዩ የቁጠባ ሂሳብ (ከፍተኛ የወለድ ምጣኔና ልዩ የብድር አገልግሎት የሚያስገኝ ) በስፋት ለማስተዋወቅ በልዩ ልዩ የሰርከስ ትርዒት የታጀበ ፕሮግራም በዚህ ሳምንት በእቴጌ ጣይቱ አብይ ቅርንጫፍ፣ የትነበርሽ ንጉሴ ጃክሮስ ፣ አርበኛ ከበደች ስዩም ገርጂ ቅርንጫፎች እያካሄደ ይገኛል ፡፡

ስላንቺን በልዩ መልኩ የማስተዋወቅ ዘመቻ በቀጣይ በዘሚ የኑስ ፊጋ ፣ሎሬት ሲስተር ጥበበ ማኮ ሰሚት፣ሀና ማሪያም እና ፀሀይ ይትባረክ ለቡ ቅርጫፎቻችን እንደሚካሄድ ልናሳውቃችሁ እንወዳለን፡፡

ማን እንደ እናት !

Address

Kazanchis
Addis Ababa
18401

Opening Hours

Monday 08:00 - 18:00
Tuesday 08:00 - 18:00
Wednesday 08:00 - 18:00
Thursday 08:00 - 18:00
Friday 08:00 - 18:00
Saturday 08:00 - 18:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ENAT BANK S.C. posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ENAT BANK S.C.:

Share