11/05/2026
የአሜሪካው መከላከያ ሚኒስቴር ፔንታጎን፣ ቀደም ሲል ሚስጥር የነበሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ የዩፎ ፋይሎችን በይፋና በማስረጃ ለቋል።
እነዚህ ሰነዶች በመላው ዓለም የታዩ ክስተቶችን የሚያካትቱ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ የታዩ ያልታወቁ በራሪ አካላት ሪፖርቶችንም ይዘዋል።
ታስታውሱ ከነበር በተለያዩ ጊዜያት በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ያልተለመዱ ብርሃን ነገሮች ይታዩ ነበር። በዜና ሰምተናቸው ሙድ እየያዝን አልፈናቸው ነበር። ዛሬ ግን ዩፎዎች ሊሆኑ ይችላሉ እየተባለ ነው።
እንደ ዓለም አቀፉ የዩፎ መመዝገቢያ ማዕከል ገለጻ መሰረትም:-
* አዲስ አበባ (የካቲት 4 ቀን 2026)፦ ምሽት 4፡21 ላይ "የሦስት ማዕዘን ቅርጽ" ያለው በራሪ አካል መታየቱ ተመዝግቧል።
* ነቀምቴ (ጥቅምት 10 ቀን 2025)፦ በኦሮሚያ ክልል ነቀምቴ ከተማ አካባቢ ሌላ ያልታወቀ አካል መታየቱ ተዘግቧል።
* ሆለታ (ታህሳስ 17 ቀን 2024)፦ "ክብ ቅርጽ" ያለው ብርሃን አመንጭ አካል በሰማይ ላይ ታይቷል።
* ሞያሌ (ጥር 2025)፦ በኢትዮጵያ እና ኬንያ ድንበር አካባቢ በከፍተኛ ፍጥነት የሚጓዝ ብርሃን ታይቶ ነበር።
Source:- EZA