Masha Woreda Finance and Economic Dev't office-የማሻ ወረዳ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Masha
  • Masha Woreda Finance and Economic Dev't office-የማሻ ወረዳ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት

Masha Woreda Finance and Economic Dev't office-የማሻ ወረዳ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት ተቋማዊ መረጃዎችን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ

ይህ የማሻ ወረዳ ፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት ገጽ ዓላማዉ በወረዳዉ እየተከናወኑ እና ለወደፊት ስለሚከናወኑ የሀብት አስተዳደር እና ቁጥጥር ስራዎች ;የልማት መረጃ አሰባሰብና የስነ-ህዝብ ጉዳዮች ክንዉኖች የመሳሰሉትን ወቅታዊ መረጃዎች ተደራሽ ማድረግ ሲሆን ይህዉም የራሱ ግላዊነት እና ህጋዊ መብቶችን በማይጻጸረር መልኩ ነዉ

16/02/2024
በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርም ላይ የገንዘብ ሚኒስቴርና የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የምክክር መድረክ ተካሄደጥር 22/ 2016 ዓ.ም - በምክክር መድረኩ ላይ በመንግስት አገል...
01/02/2024

በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርም ላይ የገንዘብ ሚኒስቴርና የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የምክክር መድረክ ተካሄደ

ጥር 22/ 2016 ዓ.ም - በምክክር መድረኩ ላይ በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርም ይዘት፣ በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ፖሊሲ፣ በመንግስት ሰራተኞች ብቃት ምዘና ማዕቀፍ እና በፖሊሲው ማስፈጸሚያ ዕቅድ ላይ ለገንዘብ ሚኒስቴርና እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አመራሮችና ባለሙያዎች ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡

በዚሁ የምክክር መድረክ ላይ ከቀረበው ገለጻም የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርም ዋነኛ ዓላማ የመንግስት ተቋማትን አደረጃጀትና አሰራር በማዘመን በክህሎትና በባህሪ የበቃ የሰው ኃይል አስተዳደርና ልማትን በመዘርጋት ለተገልጋዩ ኅብረተሰብ ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት በመስጠት የሀገርን የዕድገትና የልማት ግቦች እውን ማድረግ እንደሆነ ተብራርቷል፡፡

የገንዘብ ሚኒስትር ክቡር አቶ አህመድ ሽዴ በምክክር መድረኩ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር የገንዘብ ሚኒስቴር ለመንግስት ተቋማት የካፒታልና መደበኛ በጀት በመመደብ እና ሀገራዊ ጠቀሜታ ላላቸው ፕሮጀክቶች ከተለያዩ ምንጮች ሃብት በማሰባሰብ ከፍተኛ ሚና የሚጫወት ተቋም መሆኑን አስታውሰው ሚኒስቴሩ በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርሙ ለሙከራ ትግበራ አንዱ ሆኖ በመመረጡ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል፡፡

ክቡር ሚኒስትሩ አያይዘውም ሪፎርሙን ማስፈጸም የሚችል የፕሮጀክት ጽ/ቤት በማደራጀት፣ በቂ ሃብት በመመደብ እና እቅድ በማውጣት በቶሎ ወደ ትግበራ እንገባለን ብለዋል፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር ዴኤታ ዶክተር ኢዮብ ተካልኝ በበኩላቸው ትልልቅ ሀገራዊ ሪፎርሞችን መሸከም የሚችል ጠንካራ ሲቪል ሰርቪስ እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርም ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

ሌላው በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር ዶክተር መኩሪያ ኃይሌ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርም የገንዘብ ሚኒስቴርን ጨምሮ ለሙከራ በተመረጡ ሰባት የፌዴራል ተቋማት ላይ ተግባራዊ እንደሚደረግ ጠቁመው ሪፎርሙ፤ የመንግስት ተቋማት አሰራራቸውን በማዘመን ለተገልጋዩ ኅብረተሰብ ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት እንደሚያስችል አስረድተዋል፡፡

የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ የልማት ድርጅቶች የጋራ ፎረም ውይይት በሀላላ ኬላ ሪዞርት እያካሄደ ይገኛል።የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ በክልሉ...
28/10/2023

የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ የልማት ድርጅቶች የጋራ ፎረም ውይይት በሀላላ ኬላ ሪዞርት እያካሄደ ይገኛል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የሲቪል ልማት ድርጅቶች ጋር የጋራ ፎረሙ ውይይት በሀላላ ኬላ ሪዞርት በማካሄድ ላይ ይገኛል።

የሀዘን መግለጫ                   *************በማሻ ወረዳ ፋ/ኢ/ል/ጽ/ቤት  የስራ ባልደረባ የነበሩት አቶ አክሊሉ እንደሻዉ ጮሮ ባደረባቸዉ ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተዉ ...
12/05/2023

የሀዘን መግለጫ
*************
በማሻ ወረዳ ፋ/ኢ/ል/ጽ/ቤት የስራ ባልደረባ የነበሩት አቶ አክሊሉ እንደሻዉ ጮሮ ባደረባቸዉ ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተዉ በትናትናዉ እለት ህይወታቸዉ አልፏል:: አቶ አክሊሉ በስራቸዉ ታታሪ ቅን እና ሰዉ አክባሪ የመ/ቤታችን የስራ ባልደረባ ነበሩ::መ/ቤታችን በአቶ አክሊሉ ህልፈት የተሰማዉን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰብ ለወዳጅ ዘመዶቻቸዉ እና ለስራ ባልደረቦቻቸዉ መፅናናትን ይመኛል::
መ/ቤቱ

 #እንኳን አደረሳችሁ!!
27/11/2022

#እንኳን አደረሳችሁ!!

05/10/2022

የማሻ ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት እያካሄደ ባለዉ ጉባኤ በዛሬ ዉሎዉ በወረዳዉ ፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት የቀረበዉን የ2015 በጀት አመት ረቂቅ በጀት ብር 132,634,600 አጽድቋል::

የሸካ ዞን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ*** *** *** የሸካ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የስራ ዘመን 17ኛ መደበኛ ጉባኤውን በቴፒ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።የሸካ ዞን...
22/09/2022

የሸካ ዞን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ
*** *** ***
የሸካ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የስራ ዘመን 17ኛ መደበኛ ጉባኤውን በቴፒ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።

የሸካ ዞን ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ዮሐንስ ካሳሁን ጉባኤውን በይፋ በከፈቱበት ወቅት ባስተላለፉት መልእክት መደበኛ ጉባኤያችንን እያካሄድን የምንገኝበት ወቅት በዞናችን በተለይም እንደ የኪ ወረዳና ቴፒ ከተማ ላለፉት 3 እና ከዚያ በላይ ዓመታት ተከስቶ የነበረው የፀጥታ ችግር ተቀርፎ ዞኑ ወደ ዘላቂ ሠላም የተሸጋገረበትና የልማት ግስጋሴ የጀመርንበት በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ፤ ደስ አለን ብለዋል።

ዋና አፌ ጉባኤው አክለውም የሸካ ዞን ምክር ቤትና ህዝብ በሳል የሆነ ውሳኔ በመወሰኑ የዞኑ አስተዳደር መቀመጫውን ቀድሞ ከነበረበት ማሻ ከተማ ወደ ቴፒ ተዛውሮ ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ከመጀመሩም ባለፈ ይህ ታርካዊ ውሳኔ በመወሰኑ ድርብ እድል ማለትም ቴፒ የዞን መቀመጫ በመሆኗ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ብዝሀ ዋና ከተሞች ውስጥ አንዷ ከተማ ሆና እንዲትመረጥ መወሰኑና ስራ የሚጀምሩበት ወቅት መሆኑ ጉባኤያችንን ልዩ ያደርገዋል ሲሉም አንስተዋል።

አሸባሪው ህውሓት ሠላምን አልፈልግም በማለት ለ3ኛ ጊዜ የከፈተብንን ጦርነት ለመመከት የዞኑ ህዝብ በሁሉም ዘርፍ ያሳየው ደጀንነት የሚመሰገን መሆኑን የጠቆሙት ዋና አፌ ጉባኤው ይሄው አንድነትና ትብብር በልማቱም ልደገም ይገባል ብለዋል።

ለሁለት ተከታታይ በሚቆየው መደበኛ ጉባኤ የምክር ቤቱ የ2014 አፈጻጸም፣የአስተዳደሩ የ2014 ዓ.ም አፈጻጸም፣ የከፍተኛ ፍርድ ቤት አፈጻጸም ሪፖርት እንዲሁም የ2015 ዓ.ም እቅድ የሚቀርብ ሲሆን የ2015 ዓ.ም በጀትና ልዩ ልዩ ሹመትም ቀርቦ እንደሚጸድቅ ይጠበቃል::
የሸካ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች

https://t.me/Deb

ይህ የሀገሩን ሉአላዊነት ለማስከበር  ዳር ድንምበሯን  ከወራሪ ጠላቶች ከተላላኪ ባንዳዎች ለመጠበቅ በግንባር ከጠላት ጋር እየተዋደቀ ለሚገኘዉ ለጀግናዉ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ድጋፍ የሚዉል...
18/09/2022

ይህ የሀገሩን ሉአላዊነት ለማስከበር ዳር ድንምበሯን ከወራሪ ጠላቶች ከተላላኪ ባንዳዎች ለመጠበቅ በግንባር ከጠላት ጋር እየተዋደቀ ለሚገኘዉ ለጀግናዉ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ድጋፍ የሚዉል ከሸካ ዞን ከማሻ ወረዳ ህዝብ የተበረከተ 30 የእርድ ሰንጋ ነዉ::

የማሻ ወረዳ ፉይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት ለመላዉ ወረዳችና ለከተማችን እንዲሁም ለመላዉ የሀገራችን ህዝቦች እንኳን ለ2015 አዲስ አመት አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን እየገለፀ አዲሱ ...
10/09/2022

የማሻ ወረዳ ፉይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት ለመላዉ ወረዳችና ለከተማችን እንዲሁም ለመላዉ የሀገራችን ህዝቦች እንኳን ለ2015 አዲስ አመት አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን እየገለፀ አዲሱ አመት ለሀገራችን የሰላም የብልፅግና አመት እንዲሆን ይመኛል::
መልካም አዲሰ አመት!!

11/08/2022
10/08/2022

የደቡብ ምእራብ ህዝቦች ምክር ቤት ቤቱ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መንግስት የ2015 በጀት አመት 11ቢሊየን 33 ሚሊየን 665 ሺህ 9 መቶ 67 ብር ከ 93 ሳንቲም ሆኖ የቀረበውን የበጀት አዋጅ አጸደቀ ።

*** *** ***
የመንግስት ውስን ሀብትን ከብክነት በመከላከል ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ትኩረት ሊደረግ እንደሚገባ ተገልጿል ።

በ2015 በጀት ዓመት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት ለሚከናወኑ ሥራዎችና
አገልግልቶች የሚያስፈልገውን በጀት አጽድቆ ከበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ወቅት ጀምሮ ሥራ ላይ ማዋል አስፈላጊ መሆኑን የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ወሰነች ቶማስ ገልጸዋል ።

ከማንኛውም የገቢ ምንጭ የተገኘውን ገቢ በክልሉ ለሚገኙ ዞኖችና የክልል ማዕከላት ከፋፍሎ በጀታቸውን ለመመደብ ቀመርና ሌሎች መመዘኛዎችን መሰረት በማድረግ መሠራቱንም ኃላፊዋ ገልጸዋል ።

በክልሉ የሚገኙ ዞኖች ከክልሉ በቀመር ያገኙትን ሀብት በስራቸው ላሉ ወረዳዎችና የከተማ አስተዳደሮች ፍትሀዊ በሆነ መልኩ የቀመር አሰራርና ሌሎች መመዘኛዎችን መሠረት በማድረግ በማከፋፈል ያልተማከለውን የፋይናንስ አስተዳዳር ተግባራዊ ማድረግ እንዳለባቸው ወ/ሮ ወሰነች ቶማስ ገልጸዋል ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት ከሐምሌ 01/2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም በሚፈጸመው አንድ የበጀት ዓመት ጊዜ ውስጥ ከክልሉ መንግስት ከሚሰበሰበው ገቢ ፣ከፌደራል መንግስት ድጎማ እና ከሌሎች የገቢ ምንጮች የሚሰበሰበውን ገቢ በተመለከተ

1.ከፌደራል መንግስት ግምጃ ቤት 6,400,400,905
2.የዉጭ ዕርዳታ 38,564,62.93
3.ዘላቂ ልማት ግቦች 434,765,330
4 ከክልል ገቢ 4,159,935,112

በጠቅላላዉ የፌደራል መንግስት ድጎማና የክልሉ ገቢ ድምር 11,033,665,967.93 (አስራ አንድ ቢሊየን ሰላሳ ሦስት ሚሊየን ስድስት መቶ ስልሳ አምስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ስልሳ ሰባት ከዘጠና ሶስት ሳንቲም) ሆኖ ቀርቧል።

ከአጠቃላይ በጀትም

1.ለክልል ማዕከል 2,156,495,403.93
2.ለዞኖች ጥቅል በጀት 8 ,877,170,564,00
3.ለክልላዊ ፕሮግራም 401,561,424.50
4.ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈፀሚያ 434,765,330
5.ለክልሉ መጠባበቂያ በጀት 70,000,000
ጠቅላላ 11,033,665,967.93
(አስራ አንድ ቢሊየን ሰላሳ ሦስት ሚሊየን ስድስት መቶ ስልሳ አምስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ስልሳ ሰባት ከዘጠና ሶስት ሳንቲም)መሆኑን ኃላፊዋ አቅርበዋል ።

በ2015 በጀት ዓመት ለዞኖች የተደለደለውን የቢሮ ኃላፊዋ ወ/ሮ ወሰነች ቶማስ አብራርተዋል ።

በዚህም መሠረት:_
ሀ/ካፋ ዞን 3,084,609,615.39
ለ/ቤንች ሸኮ ዞን 1,872,257,564.10
ሐ/ዳውሮ ዞን 1,786,400,664.85
መ/ሸካ ዞን 915,994,423.89
ሠ/ምዕራብ ኦሞ ዞን 733,614,847.20
ረ/ኮንታ ዞን 484,293,448.58

ሆኖ መደልደሉን ወ/ሮ ወሰነች ቶማስ ለምክርቤቱ አብራርተዋል ።

የቀረበው የ2015 በጀት ዓመት ረቂቅ አዋጅ የምክርቤት አባላት መክረውበት በሙሉ ድምጽ አጽድቀዉታል ።

Address

Sheka
Masha

Telephone

+251475580293

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Masha Woreda Finance and Economic Dev't office-የማሻ ወረዳ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share