24/05/2023
በአዳማ ጉምሩክ ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ተወርሰው የሚገኙ የተለያዩ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎች ፣ የመገናኛ እና የኮምፒውተር እቃዎች ፣ ሸቀጣሸቀጥ ፣ የሴት ስፖርት ጫማ ፣ ብዛት ያላቸው ሞባይሎች ፣ ኮስሞቲክስ ፣ የህንፃ መሣሪያዎች እና 123 ሞተር ሳይክሎችን በግልፅ ጨረታ እንዲሁም አንድ ተሽከርካሪ እና 2 ሞተር ሳይክሎችን በሃራጅ ጨረታ ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋ
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የግልፅ ጨረታ ቁጥር 14 እና ሃራጅ ቁጥር 14/2015
በአዳማ ጉምሩክ ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ተወርሰው የሚገኙ የተለያዩ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎች፣የመገናኛ እና የኮምፒውተር እቃዎች፣ሸቀጣሸቀጥ፣የሴት ስፖርት ጫማ፣ብዛት ያላቸው ሞባይሎች፣ኮስሞቲክስ፣የህንፃ መሣሪያዎች እና 123 ሞተር ሳይክሎችን በግልፅ ጨረታ እንዲሁም አንድ ተሽከርካሪ እና 2 ሞተር ሳይክሎችን በሃራጅ ጨረታ ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
በመሆነም፡
በአዳማ ጉ/ኮ/ቅ/ጽ/ቤት ለጨረታ በቀረቡት ዕቃዎች ላይ ለመወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች በጨረታ ከሚሸጠው ዕቃ ጋር ተዛማጅነት ያለው የታደሰ ንግድ ፈቃድ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት፤ የዘመኑን ግብር የከፈለ ስለመሆኑ ክሊራንስ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ እንቅስቃሴዎችን ያሳወቁበት በቅርብ ጊዜ የተሰጣቸው፣ የምስክር ወረቀት እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥሩን ከመጫረቻ ሰነዱ ጋር ተያይዞ በፖስታ በማሸግ ለግልፅ ጨረታ በተዘጋጀውን ሳጥን ውስጥ ማስገባት እና ለሃራጅ ጨረታ ጨረታው በሚካሄድበት ቀን ማቅረብ ይኖርበታል።
በተራ ቁጥር 1 ላይ የተጠቀሰው ቢኖርም መነሻ ዋጋቸው ከ500 ሺህ ብር በታች የሆኑ ዕቃዎችን ለመግዛት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ አያስፈልግም።
በተራ ቁጥር 1 እና 2 የተጠቀሱት መስፈርቶች ቢኖሩም ሞተር ሳይክል እና ተሽከርካሪ ላይ ማንኛውም እድሜው ከ18 ዓመት በላይ የሆነ ኢትዮጵያዊ የቀበሌ መታወቂያ በመያዝ ያለ ቅድመ ሁኔታ ጨረታው ላይ መሳተፍ ይችላል።
የግልጽ እና የሃራጅ ጨረታ ሰነዱን የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ሙሉ ቀን በስራ ሰዓት እና ቅዳሜ ጠዋት ከ2፡00-6፡00 ሰዓት በአዳማ ከተማ በከልቻ ትራንስፖርት ኢማ ግቢ ውስጥ በሚገኘው የቅ/ጽ/ቤቱ የገቢ ሂሳብና ዋስትናዎች አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 11 የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ) በመግዛት በጨረታ የወጡትን ዕቃዎችን ማየት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
በግልጽ ጨረታ የሚሳተፉ ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው ለእያንዳንዱ ምድብ ለዕቃዎቹ የሰጡትን ዋጋ አምስት በመቶ (5%) እና በሃራጅ ጨረታ ለምትወዳደሩ ማለትም ለምድብ 1 ተሽከርካሪ 190,000 እና ለምድብ 2 ሞተር ሳይክል ለእያንዳንዳቸው ብር 5,000 በባንክ በተመሰከረለት (CPO) Customs Commission Adama Branch Office ስም በማሰራት ለግልፅ ጨረታ በተራ ቁጥር 1 ላይ ከተጠቀሱት ሰነዶች ጋር በማያያዝ ሳጥን ውስጥ እንድታስገበ እንዲሁም ለሃራጅ ጨረታ ጨረታው በሚካሄድበት እለት ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል።
በጨረታ ሽያጩ የእቃው አስመጪ ወይም ቤተሰብ የነበሩ ሰዎች መሳተፍ አይችሉም።
በግልጽ ጨረታ ለሽያጭ ለቀረቡት እቃዎች የጨረታ ሳጥኑ በሚገኝበት የቅ/ጽ/ቤቱ የውርስ መጋዘን አስተዳደር የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 21 ድረስ በመሄድ በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስፈልገውን የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተመሰከረለት CPO፣ የጨረታ ሰነዱን እና በተራ ቁጥር 1 ላይ ከተጠቀሱት ሌሎች ሰነዶች ጋር በፖስታ በማሸግ ሳጥኑ ከመዘጋቱ በፊት ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
በጨረታ ለመሸጥ የወጡት እቃዎች በአዳማ ከተማ በከልቻ ትራንስፖርት አ.ማ. ግቢ መጋዘን ቁጥር 5 እና መጋዘን ቁጥር 10 (ሜዳ ላይ) በሚገኘው በቅ/ጽ/ቤቱ ስለሚገኙ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ
ለግልፅ ጨረታ ባሉት 7 ተከታታይ ቀናት አየር ላይ ከዋለ በኋላ ሳጥኑ በስምንተኛው ቀን 4:00 ሰዓት ታሽጐ በ4፡15 ሰዓት የሚከፈት ሲሆን፤ ነገር ግን ስምንተኛው ቀን በበዓል ወይም እሁድ ቀን የሚውል ከሆነ ጨረታው የሚካሄደው በተመሳሳይ ሰዓት በሚቀጥለው የስራ ቀን ይሆናል።
የሃራጅ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት አየር ላይ ከዋለ በኃላ በስድስተኛው ቀን 4:00 ሰዓት ላይ የሚከፈት ሲሆን፤ ስድስተኛው ቀን በዓል ወይም እሁድ ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን የሚሄድ ይሆናል።
የግልጽ ጨረታ ሳጥኑ የሚከፈትበት ቦታ ቅ/ጽ/ቤቱ በሚገኝበት በአዳማ ከተማ በከልቻ ትራንስፖርት ኢማ ግቢ በሚገኘው የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲሆን ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል ሆኖም ተጫራቾች ካልቀረቡ ታዛቢዎች ባሉበት የጨረታ ሳጥነ ይከፈታል።
አሸናፊው ተጫራቾች ለጨረታው ጋር ዋስትና ያስያዙት CPO ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች ደግሞ የጨረታው ውጤት በተገለፀ በ3 / ሶሰት/ የስራ ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል።
አሸናፊው ተጫራቾች ማሸነፋቸውን በማስታወቂያ ከተገለፀላቸው ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ገንዘብ ገቢ በማድረግ እቃውን መረከብ ይኖርባቸዋል።
ለጨረታ የቀረቡት እቃዎች ሽያጫቸው የሚፈፀመው ባሉበት ሁኔታ ስለሆነ ተጫራቾች ሌላ ተመሳሳይ ወይም ተጨማሪ እቃ መጠየቅ አይችሉም።
ከላይ በተ/ቁ 11 ላይ በተገለፁት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት (CPO) ለመ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሜ ለሽያጭ ይቀርባል።
ማንኛውም ተጫራች 100 ብር ሰነድ የገዛበትን ደረሰኝ ለግልፅ ጨረታ ከሌሎች ሰነዶች ጋር አያይዞ በጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ያለበት ሲሆን ፤ ለሃራጅ ጨረታ ጨረታው በሚካሄድበት ዕለት ከሌሎች ሰነዶች ጋር ይዞ መገኘት አለበት።
ቅ/ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥሮች፡- 022-111-8429 እና 022-211-8925 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
በአዳማ ጉምሩክ ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት