02/10/2018
ጌታቸው አሰፋ ለፍርድ ይቅረብልን
ሼር በማድረግ ድምጻችንን እናሰማ
ፍትህ እየተንጋለለ ነው። የቀድሞ ደህንነት መስሪያ ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው አሰፋ የበርካታ ወግኖቻችንን ጥፍር ያስነቀሉ , እግር ያስቆረጡ , ያስገረፉ እና ያስገደሉ በርካቶችን ያሳደዱ ሴት እህቶቻችንን ያስደፈሩ አረመኔ ሰው ናቸው ይህ ሁሉ ሆኖ አቶ ጌታቸው በህግ ይጠየቃሉ ተብሎ ሲጠበቅ ይባስ ብሎ ለኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ተመረጡ። ፍትህ ኢትዮጵያ ውስጥ እያደር እየተንሸዋረረች ነው። አቶ አብዲ ኢሌ ታስረው የአቶ አብዲ አጋፋሪ ጌታቸው አሰፋ ለሹመት መታጨቱ የህግ የበላይነትን ጥያቄ ውስጥ ይከተዋል። የዶ/ር አብይ መንግስት ህዝብ ከጎኑ ስላሰለፈ ሳይውል ሳያድር አቶ ጌታቸውን ለፍርድ ያቅርብልን። የተበዳዮች ነብስ ትጮሀለች , ደማቸው ይንተከተካል ፍትህ ! ፍትህ ! ፍትህ ! ሼር በማድረግ ድምጻችንን እንሰማ።
ለፈጣን መረጃ #ፔጁን ላይክ ያድርጉ