Addis Ababa Saving and Credit Cooperative Federation /Ltd/ - aacssf

Addis Ababa Saving and Credit Cooperative Federation /Ltd/ - aacssf Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Addis Ababa Saving and Credit Cooperative Federation /Ltd/ - aacssf, Financial service, Addis Ababa.

Addis Ababa Savings and Credit Cooperative Federation; is a federation established since January 2013, comprising two savings and credit cooperative unions and the basic savings and credit cooperative societies.

አዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ ሁለት ቁጠባና ብድር ኀብረት ሥራ ዩኒየኖች የተመሠረተው ፤ የአዲስ አበባ ቁጠባና ብድር ኀብረት ሥራ ፌዴሬሽን ፤ ከ460 በላይ ማኀበራት ፤ ከ370 ሺ በላይ አባላት...
27/05/2026

አዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ ሁለት ቁጠባና ብድር ኀብረት ሥራ ዩኒየኖች የተመሠረተው ፤ የአዲስ አበባ ቁጠባና ብድር ኀብረት ሥራ ፌዴሬሽን ፤ ከ460 በላይ ማኀበራት ፤ ከ370 ሺ በላይ አባላት እና ከ10 ቢሊየን ብር በላይ ቁጠባን በማሰባሰብ ፤ ካፒታሉን እያሳደገ ይገኛል ።

የአዲስ አበባ ቁጠባና ብድር ፌዴሬሽኑ ፤ በዋነኝነት ከሁለቱ ዩኒየኖች ጋር በመናበብ ፤ የጋራ ዕቅዶችን በማቀድ ፤ በአዋጁ የተቀመጠለትን ተግባር እና ኃላፊነቶችን ከአስራ አንዱም ክፍለ ከተማ ኀብረት ሥራ ጽ/ቤቶች እንዲሁም በአዲስ አበባ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን ፤ ከፋይናንስ ኀብረት ሥራ ልማት ዳይሬክቶሬት ጋር በቅርበት እየሰራ ይገኛል ።

የፌዴሬሽኑን የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች ይቀላቀሉ፤

የቴሌግራም (Telegram)፡ - https://t.me/AASCCF

ፌስ-ቡክ (Facebook)፡ - https://web.facebook.com/profile.php?id=61576061610650

የዋትስ-አፕ (WhatsApp)፡ - https://chat.whatsapp.com/IS7DCijxDDn6DRqEeJoR6q

”Empowering members to drive big change"

ዒድ ሙባረክ !እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል አደረሳችሁ።በዓሉ የደስታ፣ የጤና ፣ የመተሳሰብና የሰላም እንዲሆን እንመኛለን።አዲስ አበባ ቁጠባና ብድር ፌዴሬሽን
27/05/2026

ዒድ ሙባረክ !

እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል አደረሳችሁ።

በዓሉ የደስታ፣ የጤና ፣ የመተሳሰብና የሰላም እንዲሆን እንመኛለን።

አዲስ አበባ ቁጠባና ብድር ፌዴሬሽን

አዲስ ምዕራፍ የከፈተው የኀብረት ሥራ አዋጅ ማሻሻያ******የኅብረት ሥራ ማሻሻያ አዋጅ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሙሉ ድምፅ መፅደቁ ለዘርፉ ታሪካዊ እመርታ ነው።የማሻሻያ አዋጁ ኀብረት ...
22/05/2026

አዲስ ምዕራፍ የከፈተው የኀብረት ሥራ አዋጅ ማሻሻያ
******
የኅብረት ሥራ ማሻሻያ አዋጅ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሙሉ ድምፅ መፅደቁ ለዘርፉ ታሪካዊ እመርታ ነው።

የማሻሻያ አዋጁ ኀብረት ሥራን ከለውጡ ጋር አብሮ የሚራመድ፣ ዘመኑን የዋጀ እና ሀገራዊ የልማት ተልዕኮዎችን የሚያሳካ ዘርፍ ለማድረግ ምቹ ሁኔታ የፈጠረ ነው።

ኀብረት ሥራን ከባህላዊ የማኅበር አስተሳሰብ ወደ ዘመናዊ የኢንቨስትመንትና የስራ ፈጠራ ተቋምነት የሚያሸጋግር አዲስ አቅጣጫ ያስቀመጠ ነው።

ማህበራቱ ከግሉ ዘርፍ ጋር በኢንቨስትመንት እንዲሰሩ፣ አደረጃጀታቸው እንዲጠናከር፣ በተማረ የሰው ኃይል እንዲመሩ እና የኦዲት ተደራሽነት እንዲያድግ የሚያስችል ነው።

በተለይም ማህበራት ከአባላት ውጭ ሼር እንዲሸጡ መፍቀዱ በዘርፉ ታሪካዊ ለውጥ ነው። ይህም ማህበራት ካፒታል ለማፍራት፣ ቴክኖሎጂ ለመጠቀም እና ተወዳዳሪ ቢዝነስ ለመገንባት አዲስ ዕድል ይፈጥራል።

አዲሱ አዋጅ ማህበራት በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍሎች ቅርንጫፎች ከፍተው አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ሰፊ ዕድል ይፈጥሯል።

ይህም ማኅበራቱ ያጋጥማቸው የነበረው የስራ ቦታ ገደብ በማንሳት በነፃነትና በሰፊው እንዲንቀሳቀሱ የሚያስችል ነው።

እንዲሁም አዋጁ ሴቶች፣ ወጣቶች እና አካል ጉዳተኞች በራሳቸው እንዲደራጁ ከመፍቀዱ ባለፈ፣ በሌሎች ማህበራት ውስጥ በአመራር ደረጃ የተወሰነ ድርሻ እንዲኖራቸው መደንገጉ የተሳትፎ ፍትሕን የሚያጠናክር ነው።

ከዚህ በፊት በሕግ በግልጽ ያልተደነገጉ የኢንስፔክሽንና የሕግ ማስከበር ሥርዓቶችም በአዲሱ አዋጅ ተካተዋል።

በአጠቃላይ የተሻሻለው አዋጅ፦
🔹 የማህበራትን አደረጃጀትና አመራር ያጠናክራል
🔹 የፋይናንስ ተደራሽነትን ያሳድጋል
🔹 ከግሉ ዘርፍ ጋር የኢንቨስትመንት ትስስር ይፈጥራል
🔹የሴቶች፣ ወጣቶችና አካል ጉዳተኞች ፍትሀዊ ተሳትፎ ያጠናክራል
🔹 የኦዲትና የቁጥጥር ስርዓትን ዘመናዊ ያደርጋል
🔹 ግልፅነትንና ተጠያቂነትን ያጠናክራል
🔹 የአባላትን መብትና ጥቅም በሕግ ያስከብራል

ቀጣዩ ስራ የማስፈፀሚያ ደንብ ማፀደቅና ከወረቀት ወደ ተግባር በማውረድ የኀብረት ሥራ ማህበራት እውነተኛ አቅም እንዲገለጥ ማድረግ ነው።

ጠንካራ የሕግ ማዕቀፍ = በመርህ የሚመራ ኀብረት ሥራ = ጠንካራ ማኅበራዊ ኢኮኖሚ!

18/05/2026

በአዲሱ የአዋጅ ቁጥር 1416/2018 (በ2026 እ.ኤ.አ የጸደቀው) ውስጥ የተነሱት ዋና ዋና የለውጥ ሐሳቦች የኅብረት ሥራ ማኅበራትን (በተለይም የቁጠባና ብድር ማኅበራትን - SACCOs) ከቀላል የገንዘብ ማከማቻነት ወደ ትላልቅ የኢንቨስትመንት ተቋማት (Investment Empires) የሚቀይሩ ናቸው።
በአዋጁ ውስጥ የተነሱትና ማኅበራቱን "የፋይናንስ ጡንቻ" የሚያገኑባቸው 4 ዋና ዋና ስትራቴጂካዊ ሐሳቦች እና ትርጉማቸው እንደሚከተለው ተጠቃለዋል፦

1. የካፒታል አቅምን በውጭ ኢንቨስትመንት ማሳደግ
የተነሳው ሐሳብ፦ ማኅበራት ከአባሎቻቸው ውጪ ካሉ ግለሰቦች ወይም ድርጅቶች እስከ 10% የሚደርስ የካፒታል ድርሻ (Shares) መሸጥና መሰብሰብ ይችላሉ።
ትርጉሙ፦ ቀደም ሲል ማኅበራት በአባላት አነስተኛ ቁጠባ ብቻ የተወሰነ አቅም ነበራቸው። አሁን ግን ከውጭ በሚገባ ከፍተኛ ካፒታል አማካኝነት ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ለመግዛት፣ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን ለመቅረጽና ፈጣን ዕድገት ለማስመዝገብ የሚያስችል የፋይናንስ አቅም ይፈጥራሉ።

2. የገበያ ወሰንን ወደ ሀገር አቀፍ ደረጃ ማሳደግ
የተነሳው ሐሳብ፦ ማኅበራት በአንድ ቀበሌ ወይም አካባቢ ብቻ ሳይወሰኑ በመላው ሀገሪቱ ቅርንጫፎችን መክፈት እና በብሔራዊ ደረጃ መወዳደር ይችላሉ።
ትርጉሙ፦ ይህ አሠራር ማኅበራቱን ከተወሰነና ጠባብ ገበያ (Red Ocean) በማውጣት፣ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ደንበኞችንና ሰፊ የገበያ ዕድሎችን (Blue Ocean) እንዲያገኙ መንገድ ይከፍታል።

3. የጋራ ቢዝነስ እና ስልታዊ ሽርክና (Joint Venture)
የተነሳው ሐሳብ፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራት ከግል ኩባንያዎችና ከሌሎች ባለሀብቶች ጋር በጋራ በመሆን ፋብሪካዎችን፣ የትራንስፖርት ድርጅቶችን ወይም የዲጂታል ባንክ አገልግሎቶችን ማቋቋም ይችላሉ።
ትርጉሙ፦ ማኅበሩ ከቁጠባ ባለፈ ሰፊ የቢዝነስ ግዛት (Empire) እንዲገነባ ያደርገዋል። ይህ ሽርክና ለአባላቱ ከፍተኛ የትርፍ ድርሻ (Dividend) የሚያስገኝ ከመሆኑም በላይ፣ ለኅብረተሰቡ ሰፊ የሥራ ዕድል ይፈጥራል።

4. የረጅም ጊዜ የፋይናንስ መረጋጋት (የ6 ወር ደንብ)
የተነሳው ሐሳብ፦ አንድ አባል ከማኅበሩ ድርሻውን ወይም ጥሬ ገንዘቡን አውጥቶ ለመውጣት ሲፈልግ የ6 ወር የቅድሚያ ማሳወቂያ ጊዜ (Notice Period) መጠበቅ አለበት።
ትርጉሙ፦ ይህ ሕግ ለማኅበራቱ ትልቅ የካፒታል ዋስትና ይሰጣል። አባላት በፈለጉት ጊዜ ገንዘብ ይዘው ስለማይወጡ፣ ማኅበሩ የሰበሰበውን ፈንድ ሳይሰጋ እንደ ሕንጻ ግንባታ፣ ማሽን ግዢና መሰል የረጅም ጊዜ የኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ እንዲያውለውና የተረጋጋ የፋይናንስ አቅም እንዲኖረው ያደርጋል።

ባጭሩ፦ አዋጅ 1416/2018 የኢትዮጵያን የኅብረት ሥራ ማኅበራት የሕግ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን፣ በፋይናንስ ገበያው ውስጥ እንደ ትላልቅ ባንኮችና ኮርፖሬሽኖች በከፍተኛ አቅም መወዳደርና ኢንቨስት ማድረግ የሚችሉበትን "ስትራቴጂካዊ መሣሪያ" በእጃቸው አስታጥቋቸዋል።

16/05/2026


*

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ባካሄደው 6ኛው ዙር፣ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 21ኛ መደበኛ ስብሰባው፣ የኅብረት ሥራ ማሻሻያ አዋጅን በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው፣ የኅብረት ሥራ ማህበራት ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ሰለሞን ላሌ ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ ያቀረቡ ሲሆን፣ የተሻሻሉ ጉዳዮችን እና በማሻሻያው በርካታ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት መሆኑን በዝርዝር ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

ረቂቅ አዋጁም በተበታታነ ሁኔታ በተለያየ እርከን ተደራጅተው ያሉና ውጤታማ ያልሆኑ ብዙ ቁጥር ያላቸው የኅብረት ሥራ ማህበራት ሰብሰብ ብለው በመደራጀትና ድግግሞሽን በማስቀረት ትርፋማ ለመሆንና የአባላቱን ተጠቃሚነት ከፍ በማድረግ አዳዲስ አባላት በማኅበራቱ ተሳታፊ የሚሆኑበትን የአሰራር ሥርዓት የሚዘረጋ መሆኑን ገልጸዋል።

በማጠቃለያውም፣ የኀብረት ሥራ ማህበራት አዋጅ ቁጥር 985/2018 ማሻሻያ 1416/2018 በሚል ምክር ቤቱ ማሻሻያ አዋጁን በሙሉ ድምፅ አፅድቋል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ፣ የኅብረት ሥራ ማህበራት በሪፎርሙ የተለዩ የአሰራር፣ የአደረጃጀት፣ የሰው ሃይል፣ የፋይናንስ ተደራሽነት፣ የገበያ ተወዳዳሪነት እንዲሁም የኅብረት ሥራ ማህበራትን ነፃነት የሚጋፉ ችግሮችን ለመፍታት እና ማኅበራት በተገቢው ሁኔታ ተልዕኳቸውን እንዲያሳኩ ተግዳሮቶችን በህግ ማዕቀፍ ለመፍታት በመታመኑ:- ነባሩን የኅብረት ሥራ ማህበራት አዋጅ ቁጥር 985 /2009 ወቅቱን የዋጀ ለማድረግ፣ ብሎም ሪፎርሙን መሬት ለማውረድ በሚያስችል አግባብ አዋጁን ለማሻሻል ብርቱ ጥረት ሲደረግ መቆየቱ ይታወሳል።

አዋጁ መፅደቁም፣ ኮሚሽኑ እያካሄደ ላለው ሪፎርም ጉልህ አቅም የሚፈጥር ሲሆን በቀደሙት ጊዜያት የነበሩ እና ማኅበራትን ከግዜው ጋር እኩል አላራምድ ያሉ የአዋጁ አንቀፆችን ዘመኑ በሚጠይቀው እና ሃገራዊ ተልዕኮዎችን አብሮ ማሳካት በሚቻልበት አግባብ እንዲሻሻሉ ተደርጓል፡፡

በዚህም ኮሚሽኑ መላውን የኅብረት ሥራ ቤተሰብ ብሎም ባለድርሻ አካላትን እንኳን ደስ ያላችሁ እያለ፣ ለአዋጁ መሳካት ቁልፍ ሚና ለተጫወቱ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ ማኅበራት፣ የዘርፉ አመራሮች እና ፈፃሚዎች ላቅ ያለ ምስጋና አቅርቧል፡፡

የተሻሻለው አዋጅም ተጨባጭ ውጤት ማምጣት የሚችለው መሬት ላይ ወርዶ በስራ ላይ መዋል ሲችል በመሆኑ፣ ለተግባራዊነቱ ሁሉም የኅብረት ሥራ ቤተሰብ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጥሪ ተላልፏል፡፡

የቁጠባና ብድር ኀብረት ሥራ ፌዴሬሽኑን የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎች እንዲደርስ ሼር በማድረግ፤ የፌዴሬሽኑን መረጃዎች ለሁሉም እንዲዳረስ ያድርጉ ፤የቴሌግራም (Telegram)፡...
11/03/2026

የቁጠባና ብድር ኀብረት ሥራ ፌዴሬሽኑን የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎች እንዲደርስ ሼር በማድረግ፤ የፌዴሬሽኑን መረጃዎች ለሁሉም እንዲዳረስ ያድርጉ ፤

የቴሌግራም (Telegram)፡ - https://t.me/AASCCF

ፌስ-ቡክ (Facebook)፡ - https://web.facebook.com/profile.php?id=61576061610650

የዋትስ-አፕ (WhatsApp)፡ - https://chat.whatsapp.com/IS7DCijxDDn6DRqEeJoR6q

”Empowering members to drive big change"

በከተማችን የሚገኙ የቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት ውስጥ በስፋት ከሚታዩ ችግሮች መካከል፡ -• የዓቅም ማነስ ማለትም በሂሣብ አያያዝ፤ በአመራር ብቃት እንዲሁም የኅብረት ሥራ ፅንሰ ሃሳ...
07/03/2026

በከተማችን የሚገኙ የቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት ውስጥ በስፋት ከሚታዩ ችግሮች መካከል፡ -

• የዓቅም ማነስ ማለትም በሂሣብ አያያዝ፤ በአመራር ብቃት እንዲሁም የኅብረት ሥራ ፅንሰ ሃሳብ ዙሪያ የግልፀኝነት ችግር፤

• ለብድር የሚሆን የገንዘብ እጥረት (Liquidity Financing) ችግር፤ በውስን ቦታ የገንዘብ ክምችት ሲኖር በሌላ ቦታ እጥረት መኖሩ፤

• ዘመናዊ የአሠራር ሥርዓትን (Digitalization) ከመከተል አንፃር የሚታይ ችግር፤

ዋና ዋናዎቹ ሲሆኑ የአዲስ አበባ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ፌዴሬሽን፤ በበጀት ዓመቱ ከላይ የተዘረዘሩትንና ሌሎች የማኅበራቱን ችግሮች በመለየት፤ ከአዲስ አበባ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን እና ከሚመለከታቸው የባለ-ድርሻ አካላት ጋር በመሆን አበክሮ እየሠራ ይገኛል፡፡

”Empowering members to drive big change"

እንኳን ለአባቶቻችንና እናቶቻችን የሀገር ፍቅር፣ የጽናት እና አይነኬነት ተምሳሌት፣ ለጥቁር ሕዝቦች ደግም የአሸናፊነት ብርሃን ለሆነው ለአደዋ በዓል አደረሰን ፤ አደረሣችሁ !!!አዲስ አበባ ...
02/03/2026

እንኳን ለአባቶቻችንና እናቶቻችን የሀገር ፍቅር፣ የጽናት እና አይነኬነት ተምሳሌት፣ ለጥቁር ሕዝቦች ደግም የአሸናፊነት ብርሃን ለሆነው ለአደዋ በዓል አደረሰን ፤ አደረሣችሁ !!!

አዲስ አበባ ቁጠባና ብድር ፌዴሬሽን ፤

የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኀብረት ሥራ ማህበራት (SACCO) ለአባላትና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ያላቸው ፋይዳ፡- 1) ለአባላት የሚሰጡ ፋይዳ1.  ቀላል ብድር አገልግሎት፡- SACCO ዎች አባላትን...
23/02/2026

የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኀብረት ሥራ ማህበራት (SACCO) ለአባላትና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ያላቸው ፋይዳ፡-

1) ለአባላት የሚሰጡ ፋይዳ

1. ቀላል ብድር አገልግሎት፡- SACCO ዎች አባላትን በዝቅተኛ ወለድ እና በቀላል ሂደት ብድር ይሰጣሉ። ይህ ትንሽ ንግድ መጀመር፣ የቤት ግንባታ፣ የትምህርት ወጪ እና አስቸኳይ ፍላጎቶች ለመሟላት ይረዳል።

2. ዝቅተኛ የብድር ወለድ፦ ከባንኮች ጋር ሲነጻጸር ማህበራቱ አነስተኛ ወለድ ያስከፍላሉ፤ ይህም አባላት በቀላሉ ብድር አግኝተው ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ ይረዳቸዋል።

3. ቀላል የብድር መስፈርቶች፦ በማህበራቱ ውስጥ ብድር ለማግኘት የሚጠየቁት መስፈርቶች (ለምሳሌ ዋስትና) ከአባላቱ አቅም ጋር የተመጣጠኑ ናቸው።

4. ቁጠባን ማበረታታት፡- አባላት በየወሩ ቁጠባ በማድረግ የቁጠባ ባህል ያዳብራሉ፣ የግል ፋይናንስ አስተዳደር ይሻሻላል።

5. ትርፍ መካፈል (ዲቪደንድ)

6. SACCO ዎች በዓመት መጨረሻ ከተገኘ ትርፍ ለአባላት ዲቪደንድ ያካፍላሉ፣ ይህም ተጨማሪ ገቢ ይፈጥራል።

7. የራስ አስተዳደር መብት

8. አባላት በውስጥ ምርጫ እና ውሳኔ ሂደት ይሳተፋሉ፤ እያንዳንዱ አባል “አንድ ድምፅ” መርህ ይኖረዋል።

9. የማህበራዊ ድጋፍ

10. በአባላት መካከል እርዳታና መተባበር ይጠናከራል፤ አንዳንድ SACCO ዎች የመዋጮ ፈንድ ይኖራቸዋል።

2) በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ያላቸው ፋይዳ

1. የአካባቢ ኢኮኖሚ እድገት፡- ተሰብስቦ የሚከማች ቁጠባ ወደ ብድር ተመልሶ በአካባቢ ንግድ እና ሥራ ፍጠር ላይ ይውላል።

2. የቁጠባ መጠን መጨመር፡- የሀገር ውስጥ ቁጠባ መጠን በመጨመር ኢኮኖሚያዊ መዋቅር ይጠናከራል።

3. ድህነት መቀነስ፡- በትንሽ እና መካከለኛ ንግዶች ላይ የሚሰጥ ድጋፍ ገቢ ያመነጫል፣ የቤተሰብ ኑሮ ይሻሻላል።

4. የህብረት ሥራ ባህል ማጠናከር፡- የመተባበር እና የእርስ በርስ እምነት ባህል ይጠናከራል፣ ይህም ለሌሎች ልማት ፕሮጀክቶች መሠረት ይሆናል።

5. የሀገር ውስጥ ካፒታል መፍጠር፦ በየደረጃው የሚሰበሰበው ጥቃቅን ቁጠባ ተከማችቶ ለትላልቅ ኢንቨስትመንቶች የሚውል ካፒታል እንዲፈጠር ያደርጋል።

6. የሥራ ዕድል ፈጠራ፦ አባላት ከማህበራቱ በሚወስዱት ብድር ወደ ተለያዩ የንግድ ዘርፎች (ግብርና፣ ንግድ፣ አገልግሎት) በመሰማራት ለራሳቸውና ለሌሎች የሥራ ዕድል ይፈጥራሉ።

7. የዋጋ ንረትን መከላከል፦ ህብረተሰቡ ገንዘቡን እንዲቆጥብ በማድረግ በገበያ ውስጥ ያለውን ያልተገባ የገንዘብ ዝውውር በመቀነስ የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት ይረዳሉ።

8. የፋይናንስ አካታችነት (Financial Inclusion)፦ በገጠርና በከተማ ዳርቻዎች የሚገኙ፣ የባንክ አገልግሎት የማይደርሳቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የፋይናንስ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋሉ።

የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኀብረት ሥራ ማህበራት በከተሞችና በገጠር አካባቢዎች ፈጣን እድገት እያሳዩ ናቸው። በየኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን መመሪያና ቁጥጥር ስር ብዙ ሺህ ማህበራት ተመዝግበው እየሰሩ ናቸው። እነዚህ ማህበራት በተለይ ለወጣቶች፣ ለሴቶች እና ለትንሽ ንግድ ተቋማት ዋና የፋይናንስ ምንጭ ሆነዋል።

የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኀብረት ሥራ ማህበራት ለአባላት የፋይናንስ ነፃነት እድል ሲፈጥሩ፣ በአጠቃላይ ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት፣ ሥራ ፍጠር እና ድህነት መቀነስ ትልቅ ሚና ያጫውታሉ።

የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት፡ የኢኮኖሚ ዋስትና እና የአባላት ተጠቃሚነት
የገንዘብ ቁጠባና ብድር ማህበራት "በጋራ በመቆጠብ ለጋራ እድገት" በሚል መርህ የሚመሩ፣ አባላት የራሳቸውን ካፒታል አሰባስበው ለራሳቸው ብድር የሚያቀርቡባቸው ተቋማት ናቸው።

ምንጭ ፦ አዲስ አበባ ኀብረት ሥራ ኮሚሽን

አዲስ አበባ ቁጠባና ብድር ኀብረት ሥራ ፌዴሬሽን በዋነኝነት የሚሰጣቸው አገልግሎቶች፡ -  • ለማኅበራቱ እና ለዩኒየኖች ዓቅማቸውን ያገናዘበ የኦዲት እና የሥልጠና አገልግሎት መስጠት፤ • ከማ...
11/02/2026

አዲስ አበባ ቁጠባና ብድር ኀብረት ሥራ ፌዴሬሽን በዋነኝነት የሚሰጣቸው አገልግሎቶች፡ -

• ለማኅበራቱ እና ለዩኒየኖች ዓቅማቸውን ያገናዘበ የኦዲት እና የሥልጠና አገልግሎት መስጠት፤

• ከማኅበራቱ እና ከዩኒየኖቹ ዓቅም በላይ የሆኑትን ችግሮች በመለየት፤ ተግባር ተኮር ምርምር በማድረግ ጥናት በማጥናት እና በማስጠናት መፍታት፤

• ማኅበራቱና ዩኒየኖቹ ያለባቸውን የገንዘብ ትስስር ችግር (Liquidity Finance Problem) ከፋይናንስ ተቋማት እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን መፍታት፤

• በሃገር ውስጥ እና በውጪ ከሚገኙ ተመሣሣይ ተቋማት ጋር ልምድና ተሞክሮዎችን፤ ሥልጠናዎችንና ዘመናዊ አሠራሮችን በመውሰድ፤ እንዲተገበር ማድረግ፤

• የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፤ ዘመናዊ የመረጃ ማዕከል በማቋቋም፤ ለማኅበረሰቡ እና ለኅብረት ሥራ ማኀበራት ወቅታዊ መረጃዎች እንዲደርሱ ማድረግ፤

• ማኅበራቱን፤ ዩኒየኖቹን እንዲሁም የባለድርሻ አካላቱን በማካተት ዓለም አቀፍ የቁጠባና ብድር ቀን በአልን በማስተባበር እንዲከበር ማድረግ፤

• ለኀብረት ሥራ ማኀበራት እና ለዩኒየኖች የህግ ማማከር አገልግሎት መስጠት፤

Address

Addis Ababa
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Ababa Saving and Credit Cooperative Federation /Ltd/ - aacssf posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share