Gizachew Girma Ossa

Gizachew Girma Ossa CBE

እንኳን የጌታችንና የመድኃንታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት መታሰብያ በዓል አደረሳችሁ!!!**"ተፈጸመ"** የሚለው ቃል በመስቀል ላይ ከተነገሩ ሰባት ቃላት መካከል እጅግ ሚስጥራዊና የድል ...
10/04/2026

እንኳን የጌታችንና የመድኃንታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት መታሰብያ በዓል አደረሳችሁ!!!
**"ተፈጸመ"** የሚለው ቃል በመስቀል ላይ ከተነገሩ ሰባት ቃላት መካከል እጅግ ሚስጥራዊና የድል ቃል ነው። ይህ ቃል በዮሐንስ ወንጌል 19፥30 ላይ ተመዝግቧል። ቃሉን በብዙ ነጥቦችና በሰፊ ትርጉም እንደሚከተለው ልናብራራው እንችላለን፦

---

# # # **1. የትንቢቶች ፍጻሜ (Prophetic Fulfillment)**
ከመቶና ከሺህ ዓመታት በፊት ስለ መሲሁ መምጣት፣ መከራ መቀበል፣ መሞትና መነሣት የተነገሩ ትንቢቶች በሙሉ በዚህ ቃል የታሸጉ ናቸው።
* **ኢሳይያስ 53፡** "ስለ መተላለፋችን ቈሰለ" ተብሎ የተነገረው ትንቢት ፍጻሜውን አገኘ።
* **መዝሙረ ዳዊት፡** ስለ ልብሱ መታደል፣ ስለ እጅና እግሩ መቸንከር የተነገሩት ሁሉ እውነት ሆኑ።
እግዚአብሔር ለሰው ልጅ የገባው የተስፋ ቃል ሁሉ በመስቀል ላይ "ተፈጸመ"።

# # # **2. የሕግ ፍጻሜ (Legal Fulfillment)**
የብሉይ ኪዳን ሕግና ሥርዓት የሰው ልጅን ከኃጢአት ፍርድ ሊያድኑት አልቻሉም ነበር።
* ክርስቶስ ሕጉን በሙሉ በመፈጸም፣ ሕጉ በሰው ልጅ ላይ የፈረደውን የሞት ፍርድ አስወገደ።
* በደብዳቤና በሥርዓት የታሰረውን የዕዳ ጽሕፈት በመስቀል ላይ በመቸንከር አጠፋው (**ቆላስይስ 2፥14**)።

# # # **3. የመሥዋዕት ፍጻሜ (Sacrificial Fulfillment)**
ለሺህ ዓመታት ይፈስ የነበረው የእንስሳት ደም የሰውን ኃጢአት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ማጥፋት አልቻለም ነበር።
* ክርስቶስ "የእግዚአብሔር በግ" ሆኖ በመቅረብ፣ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ ፍጹም መሥዋዕት ሆነ።
* ከእንግዲህ በኋላ ሌላ መሥዋዕት አያስፈልግም፤ "ተፈጸመ" ማለት "መሥዋዕቱ ተቀባይነት አግኝቷል" ማለት ነው።

# # # **4. የቤዛነት ፍጻሜ (Redemptive Fulfillment)**
"ተፈጸመ" የሚለው የግሪክ ቃል **"Tetelestai"** ሲሆን፣ በጥንቱ የንግድ ዓለም "ዕዳው ሙሉ በሙሉ ተከፍሏል" (Paid in full) ለማለት ጥቅም ላይ ይውል ነበር።
* የሰው ልጅ በኃጢአቱ ምክንያት የነበረበት የሞት ዕዳ በክርስቶስ ደም ተከፈለ።
* ሰይጣን በሰው ልጅ ላይ የነበረው የባለቤትነት መብት አበቃ። "ተፈጸመ" ማለት "እንግዲህ ነፃ ናችሁ" ማለት ነው።

# # # **5. የድል አዋጅ (Declaration of Victory)**
ይህ ቃል የተስፋ መቁረጥ ቃል ሳይሆን፣ የኃያል አሸናፊ ጩኸት ነው።
* ሞት ተሸነፈ፣ መቃብር ተረታ፣ ሰይጣን ድል ሆነ።
* ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሆኖ "ተፈጸመ" ሲል፣ የሰው ልጅ ድል በዚያ ቅጽበት ተረጋገጠ።

# # # **6. የፍጥረት መታደስ ፍጻሜ (Re-creation)**
እግዚአብሔር በመጀመሪያ ፍጥረትን ፈጥሮ ሲጨርስ "ሁሉ መልካም ነው" ብሎ ነበር። በመስቀል ላይ ደግሞ የጠፋውን ፍጥረት መልሶ ሲያድስ "ተፈጸመ" አለ።
* አሮጌው ማንነት አብቅቶ አዲስ ማንነት ተጀመረ።
* ከእግዚአብሔር ጋር የነበረው ጥል ተወግዶ እርቅ ወረደ።

---

> "ወንድሞቼ ሆይ! ጌታ በመስቀል ላይ 'ተፈጸመ' ሲል፣ ያንተም የጭንቀት ዘመን ተፈጽሟል። ያንተም የሕመም ዘመን ተፈጽሟል።
> 1. **ዕዳ የለብህም፦** ጌታ ከፍሎታል።
> 2. **ፍርድ የለብህም፦** ጌታ ተቀብሎታል።
> 3. **ባርነት የለብህም፦** ጌታ ነፃ አውጥቶሃል።
>
> ዛሬ 'ተፈጸመ' የሚለውን ቃል ይዘህ ውጣ፤ የጀመርከው ሥራ ይፈጸማል፣ የያዝከው በረከት ይፈጸማል፣ የሕይወትህ ጉዞ በድል ይጠናቀቃል!"

---

04/04/2026

ቅዱሳኖቹ ወደ Wembley የማይጨበጥ አር-ቴታ እና አር-ሴናል ተሸንፏል

ምን እየተካሄደ እንደሆነ እጅግ ያሳዝናል
04/04/2026

ምን እየተካሄደ እንደሆነ እጅግ ያሳዝናል

02/04/2026

አሜን ተባረክልኝ

What¿︎????¿?¿
02/04/2026

What¿︎????¿?¿

31/03/2026
አይዞሽ ገለቴ Donald Trump ሆይ ሰማኽ ወይ!!!!
20/03/2026

አይዞሽ ገለቴ Donald Trump ሆይ ሰማኽ ወይ!!!!

ኢራን የዛቻ ደረጃዋን ወደ መጨረሻው ጥረት (Nuclear level) አሳድጋለች፦

“በየትኛውም የዓለም ክፍል ብትሆኑ ኢላማ እናደርጋችኋለን፤ ባለሥልጣናት፣ ፓይለቶች፣ ወታደሮች... በመዝናኛ ስፍራዎች እና በቱሪስት መዳረሻዎች ጭምር።

በምድር ላይ ለእናንተ ደህንነቱ የተጠበቀ ምንም አይነት ስፍራ አይኖርም።”

ይህ ይፋዊ ማስጠንቀቂያቸው ነው። ውጥረቱ አሁን ወደ አዲስ እና አስፈሪ ደረጃ ተሸጋግሯል።

ምንጭ፦ clashreport

ምንም የተሰጠ ማሳሰቢያ ሳይኖር በእኔ ቦታ ዋና መጋቢ ተሹሞ እኔ በጡረታ እንድወጣ የስንብት ደብዳቤ ተሰጠኝ:- ዶ/ር ፓስተር ዮሐንስ ባሳናዶ/ር ፓስተር ዮሐንስ ባሳና በኢትዮጵያ ወንጌላውያን ...
30/12/2025

ምንም የተሰጠ ማሳሰቢያ ሳይኖር በእኔ ቦታ ዋና መጋቢ ተሹሞ እኔ በጡረታ እንድወጣ የስንብት ደብዳቤ ተሰጠኝ:- ዶ/ር ፓስተር ዮሐንስ ባሳና

ዶ/ር ፓስተር ዮሐንስ ባሳና በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት የወላይታ ቀጠና የስታዲየም ቃለ ሕይወት አጥቢያ ቤተክርስቲያን መጋቢ መልእክት በመላው አለም ለሚገኙና ለሚመለከታቸው ቅዱሳን እንደሚከተለው ሃሣባቸውን አቅርበዋል።

በጌታችንና በመድኃንታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የማክበር ሰለምታዬን አቀርብላችኃለሁ፡፡

በመቀጠልም በወላይታ ሶዶ ስታዲዬም አ/ቃ/ሕ/ቤ/ያን ከ26 ዓመት አገልግሎት በኃላ የተከሰተብኝን አሉታዊ ክስተትን ለእውቀትና ለጸሎት እንዲረዳ የሚከተለውን አቀርባለሁ።

በ1967 ዓ.ም የቤተ ክርስቲያን መስሪያ ቦታ ሲመነጠር ሲደላደል ከሚሰሩ ጋር በጉልበቴ ሰርቻለሁ፤ ቤተክርስቲያን ሲሰራ ከመላ ወላይታ አጥቢያዎች የአንድ ቀን መባ በተለያዩ ጊዜያት የተሰበሰበውን ገንዘብ አብዘኛውን ሳንቲም ነበርና በትከሽዬ ተሸክሜ አምጥቼ ለሚሰሩ ኮሚቴዎች አስረክብያለሁ፤ የአዳራሹ ግንባታ ተጠናቅቆ ሲመረቅ ከአራቱ ሸማግሌዎች አንዱ ሆኘ አገልግያለው፡፡

ለተወሰኑ ወራት በወንጌላዊነት ያገለገለ ወንጌላዊ ወደ ሌላ ቦታ ሲሄድ በወንጌላዊነት ተመድቤ ብቻዬን ሌላ ተጨማሪ ወንጌላዊ ሳይኖር ከ1968 ፟እስኬ 1978 ድረስ ለአስር ተከታታይ አመታት በወንጌላዊነት አገልግያለሁ፤ መንፈሳዊ አገልግሎቶችን ሁሉ የእሁድ ጠዋት መደበኛ አምልኮ፣ የከሰዓት ከኃላ ፕሮግራም፣ ረቡዕ የሴቶች ፕሮግራም፣ ቅዳም የልጆች ትምህርት ሌሎች የተለያዩ ፕሮገራሞች ሁሉ የሚሸፈኑት በእኔ ነበር፡፡

የሚሰፈርልኝ ቀለብ በወር የጌታ እራት ቀን መባ ከአምልኮ በኃላ በሙዳይ ላይ የሚጣል ከአስራትና ከስጦታ ውጪ ፍራንክ ብቻ ይሰጠኝ ነበር፤ ከጽ/ቤት 80 ብር አድጎ 115 ብር በኃላ ይከፈለኝ ነበር፡፡ ቤተሰቤ ያለው አረካ ወርሙማ ነበርና ለቤተሰቤ ልኬ በቀረችው ፍራንክ መጠቀም የሚችለው ቁርስ፣ ምሳና እራት ዳቦ በሽይ ብቻ ነበርና ሰውነቴ እየተጎዳ ለልዩ ልዩ ህመም ይጋለጥ ነበር፣ ከርህብና ከድካም የተነሳ ለአስም፣ ለኒሞኒያ፣ ለስኩዋር፣ ለግፊት፣ ለወባና ለሌሎች ህመሞች የተጋለጥኩበት ምቾት በማጣት በእስራት በስደት ከጭንቀት የተነሳ ደርሶብኛል፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያለፍኩኝ ብዙዎችን የጋቢቻ ትምህርት አስተምሬ አጋብቻለሁ ታምመው ጸልያለው፤ ለዳኑም አመስግኛለሁ፤ በኃዜናችው አብሬ አዝኛለሁ፤ ሲደሰቱ ተደስቻለሁ፤ እኔን በአገልግሎቴ አሳዝነሄኛል ጎድተሄኛል የሚል ሰው ካለ እክሰዋለሁ ይቅርታ እጠይቀዋለው፡፡ ከቤተክረቲያናችንና ከሌላ ቦታ በተለያዩ ጸጋ የሚያገለግሉትን አገልጋዮችን ጋብዤ አምጥቼ እንዲያገለግሉ አድርግያለሁ፡፡

ይህ በእንድህ እንዳለ ከተለያዩ ሁኔታዎች የተነሳ ከሁለት አመታት ጅምሮ አልፎ አልፎ ከመጋቢነት ኃላፊነት በርፍ መልካም ነው እያልኩ ሀሳብ አቀርብ ነበር;፡ በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ከቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎ መካከል ሶስቱ ማለትም አቶ ዘለቀ፣ አቶ ጎጆሌ እና አቶ አለቃ ስሜ ወደ ቤቴ መጥተው አንተ የሚታቀርበውን ከመጋቢነት ኃላፊነት አርፋለሁ የሚትለውን ሀሳብ አንሳ እኛም አባላትም እግዚአብሔርም አንተን በዚህ ቤተ ክርስቲያን እንድትኖር እንድታገለግል እንፈልጋለን የሚል ሀሳብ ይዘን መጥተናል አሉኝ፡፡ እኔም ከባለቤቴም ጋር ተወያይተን እና ተመካክረን እሽ ሀሳባችሁን ተቀብለናል ሀሳቤን አንስቻለሁ በማለት መስማማታችንን አረጋገጥን፡፡ በፊትም ብሆን በደብዳቤ ቤተክርስቲያንን ሼኙኝ ብዬ አልጠየኩም በቃል ተነጋግረን አመስግነን ተለያየን፡፡

በሚያዝያ ወር 2017 ዓ.ም የልጀ ሰርግ ፕሮግራም ነበር፤ ይህንን ሰርግ በሚመለከት 1. በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን በ1997 ዓ.ም ተሻሽሎ በተፃፈው በእምነት አቋምና ውስጠ ድንብ ገጽ 16 አንቀጽ 3; 1.5 ጋቢቻ መፍረስና ዳግም ጋቢቻን በተመለከተ ጋቢቻ መፍረስ የሚችለው በሶስት ምክኛት ነው ይላል፡፡ 1. በሞት 2.በዝሙት እና 3. ባለማመን ምክኛት ያላመነው ወገን ጋቢቻውን ቢያፈርስ ያመነው ወገን ቤላ አማኝ ሊያገባ ይችላል ይላል፡፡ ይህ በቤተ ክርስቲያናችን ለ90 አመታት በላይ ስትመራ የኖረችበት መመሪያ እና ውስጠ ደንብ ነው፡፡ በዚህ መመሪያ መሰረት የተዳረችበት ጋቢቻ ምክኛት ቴክኒክና ታክቲክ በሞላበት ሁኔታ ተቀነባብሮ በእኔ ላይጸመ ድራማ ተካሂዶብኛል፡፡ በጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም ሽማግሎዎች ጠርተውኝ ሽኝትህን እንደት መፈጸም እንዳለብን ልንመካከር እንፈልጋለን አሉኝ፤ እኔ ወደዚህ ትላንት የመጣሁት እንግዳ ሰው ሳልሆን 26 ዓመታትን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳልል ያገለገልኩት አገልጋይ ነኝ አባላት ሁሉ ባሉቤት ጉባኤ እኔ የሚሸኝበት ሁኔታን በተመለከተ እናንተ ተናግራችሁ ቀጥኖ እኔ ተናግሬ ከአባላትም ተናግረው ሁሉም ተስማምተው ቡራኬ ስጥተው ቢሸኙኝ መልካም ነው በመባባል ተስማምተን ለህዳር 14/2018 ዓ.ም ቀጠሮ ተይዞ በጸሎት ተለያየን፡፡

በጸሎት የጠበቅንወ ቀን ደረሰ በእለቱ ከልጆቼ ሁሌቱ ከአድስ አበባ እና ከደብረዘይት ሁኔታውን ለማየት መጥተው ነበርና የተቀጠረው ቀጠሮ ምን እንደሆነ ምንም የተሰጠ መግለጫና ማሳሰቢያ ሳይኖር ፕሮግራሙ አበቃ፡፡ 14/03/2018 እየተጠበቀ እያለ ሁለት ነገሮች ሆኑ፤
1ኛ. በእኔ ቦታ ዋና መጋቢ ተሹመዋል፤
2ኛ. በ01/03/2018 የጡረታ ዝግጅት በማድረግ ከ01/05/2018 ዓ.ም ጡረታ እንድወጣ በቤተከርስቲያን የተወሰነ መሆኑን የሚገልጽ በሰብሳቢ የተፈረመ የስንብት ደብዳቤ ተሰጠኝ፡፡

ከሶስት አመት በፊት ጡረታ አለመፈለገን ነግረ ነበር ስለዚህ ለጡረታ የሚዘጋጅበትና የማስከብርበት ፍላጎት ዝግጅት የለኝም አይኖረኝምም እግዚአብሔር ዋስትናዬ ነው፡፡ ወደፈት ሙሉ እና በቂ መረጃ እስከማደርስላችሁ ድረስ ግንዛቤ እንድኖራችሁ ይህ ጽሁፍ እንድነብብ ይሁን፡፡

የልጀን ጋቢቻ በሚመለከት አንደኛ ኃላፊነቱን ወስደው ስነ ስራዓቱን የፈጸመው የደብረ ዘይት ሙሉ ወንጌል ቤተከርስቲያን ስሆን በቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ብሆንም በእምነት አቁዋምና ውስጠ ደንብ ገጽ 16 አንቀጽ 3. 1.5 ላይ በግልጽ ተቀምጡዋል፡፡ ፕሮግራሙ እንድፈጸም እኔ ለፕሮግራሙ አዳራሽ አልጠየኩም መሳሪያ አልጠየኩም በቤቴ ምሳ ብሉልን ቡና ጠጡ ከእኛ ጋር እንግዶችን ሸኙልን አልኩኝ እንጂ ሌላ የጠየኩት ነገር የለም፡፡

ቤተክርስቲያኒቱን አልበደልኩም የእግዚአብሔርን ቃል ሥልጣን አልጣስኩም በህልናዬ ንጹህ ነው፡፡ በእኔ ቦታ ለተሾመው አድሱ ፓስተር ሲሾም ጸልይ ቡራኬ ስጥ አልተባልኩም ቦታዬን አልለቅም አላልኩም አልልምም ነገር ግን በእኔ ላይ የሆነብኝ ነገር ሁኑ የሆነብኝ በእግዚአብሔርና በሰው ፍት ልክ ነው ወይ? ፍርዱን ለእናንተና ለእግዚአብሔር ሰጥቻለው፡፡ ይህንን ጽሑፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ለሚወዱኝና ለሚወዳቸው ወገኖቼ በፊታቸው ተገኝቼ የሆነውን ነገር ለመናገር እድል ባለማግኘተ እና ሁሉም ሰው ግንዛቤ እንዲኖረው መጋቢያችን ምን ሆነ ለሚሉ ወገኖቼ እውነቱን ለማሳወቅ ነው፡፡

በጌታ ወገናችሁ ነኝ
ዶ/ር ዮሐንስ ባሳና (መጋቢ)

~~~~~√~~~~~
ለዚህ ፌስቡክ ገጽ አዲስ ከሆኑ በዚህ Gizachew Girma Ossa ውስጥ በመግባት follow የሚለውን አንድ ጊዜ በመንካት አዳዲስ መረጃዎችን ያግኙ።

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Yaikob Balcha, Znash Dabara, Adu Adanech, Dawit Cheneke, ...
27/12/2025

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Yaikob Balcha, Znash Dabara, Adu Adanech, Dawit Cheneke, Papy Ashenafi, Ashebir Ashu

25/12/2025

ማንችስተር ዩናይትድ 25/26 ውድድር ዘመን ከ10 በላይ ሆኖ እንደማይጨርስ ተረጋግጧል @@@እመለሳለሁ ጠብቁኝ

Jesus is King
25/12/2025

Jesus is King

Address

Adis
Addis Ababa

Telephone

+251926468407

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gizachew Girma Ossa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gizachew Girma Ossa:

Share